عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«حُجِبَتِ النَّارُ بِالشَّهَوَاتِ، وَحُجِبَتِ الْجَنَّةُ بِالْمَكَارِهِ».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ከአቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንደተላለፈው ረሱል ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡
"ጀሀነም በፍላጎቶች ተጋረደች፤ ጀነት ደግሞ በሚጠሉ ነገሮች ተጋረደች።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ ጀሀነም ክልክልን በመዳፈርና ግዴታን ባለመወጣት የመሰሉ ነፍስያ በምትፈልጋቸው ነገሮች መሸፈኗን መከበቧን ገለፁ። በመሆኑም የነፍስያውን ፍላጎት በዚህ ረገድ የተከተለ ለጀሀነም ተገባ። ጀነት ደግሞ ትእዛዝ ላይ በመዘውተር፣ ክልከላን በመተውና በዚሁ ላይ ትዕግስት በማድረግ በመሰሉ ነፍስያ በምትጠላቸው ነገሮች መሸፈኗንና መከበቧን አብራሩ። ስለዚህም በዚህ ረገድ በቁርጠኝነት ነፍስያውን የታገለ ለጀነት የተገባ ሆነ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በስሜት ላይ ለመውደቅ ሰበብ ከሚሆኑ መሰናክሎች መካከል አስቀያሚና የተወገዘ የሆነውን ነገር ነፍስያ ወዳው እስክትዘነበልለት ድረስ ሸይጧን ማስዋቡ አንዱ መሆኑን፤
  2. ወደ ጀሀነም እሳት መዳረሻ ከመሆናቸው አንፃር ከተከለከሉ ፍላጎቶች መራቅና ወደ ጀነት የሚያደርሱ ከመሆናቸው አንፃርም የምንጠላቸው ነገሮች ላይ መታገስን መታዘዛችን ፤
  3. ነፍስያን መታገል፣ በዒባዳ ላይም መትጋት፣ በአምልኮ ዙርያ ያሉ የምንጠላቸውና የሚያስቸግሩን ነገሮች ላይም መታገስ ያለውን ትሩፋት እንረዳለን።