عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«حُجِبَتِ النَّارُ بِالشَّهَوَاتِ، وَحُجِبَتِ الْجَنَّةُ بِالْمَكَارِهِ».
[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...
ከአቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንደተላለፈው ረሱል ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡
"ጀሀነም በፍላጎቶች ተጋረደች፤ ጀነት ደግሞ በሚጠሉ ነገሮች ተጋረደች።"
Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]
ነቢዩ ﷺ ጀሀነም ክልክልን በመዳፈርና ግዴታን ባለመወጣት የመሰሉ ነፍስያ በምትፈልጋቸው ነገሮች መሸፈኗን መከበቧን ገለፁ። በመሆኑም የነፍስያውን ፍላጎት በዚህ ረገድ የተከተለ ለጀሀነም ተገባ። ጀነት ደግሞ ትእዛዝ ላይ በመዘውተር፣ ክልከላን በመተውና በዚሁ ላይ ትዕግስት በማድረግ በመሰሉ ነፍስያ በምትጠላቸው ነገሮች መሸፈኗንና መከበቧን አብራሩ። ስለዚህም በዚህ ረገድ በቁርጠኝነት ነፍስያውን የታገለ ለጀነት የተገባ ሆነ።