عن سهل بن سعد رضي الله عنه عن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«مَنْ يَضْمَنْ لِي مَا بَيْنَ لَحْيَيْهِ وَمَا بَيْنَ رِجْلَيْهِ أَضْمَنْ لَهُ الْجَنَّةَ».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ከሰህል ቢን ሰዕድ -አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና- እንደተላለፈው የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡
"በሁለት መንገጭላዎቹ መካከል እና በሁለት እግሮቹ መካከል ያሉትን (ሊጠብቅ) ዋስትና ለገባልኝ እኔም ጀነትን ዋስትና እገባለታለሁ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ አንድ ሙስሊም እነርሱን በሚገባ ከጠበቀ ጀነት የሚገባባቸው የሆኑ ሁለት ጉዳዮችን ተናገሩ።
የመጀመርያው፡ የላቀው አሏህን ከሚያስቆጣ ንግግር ምላስን መቆጠብ፤
ሁለተኛው፡ ብልትን ከብልግና መቆጠብ ነው።
ምክንያቱም አብዛኛውን ጊዜ ወንጀል የሚፈፀምባቸው እነዚህ ሁለቱ አካላት ስለሆኑ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ምላስንና ብልትን መጠበቅ ጀነት ለመግባት ሰበብ መሆኑን እንረዳላን።
  2. ምላስና ብልት ተለይተው የተጠቀሱበት ምክንያት የሰው ልጅ በዱንያውም ሆነ በአኼራው ለሚመጣበት መከራ ዋነኛ ምንጮች ሁለቱ በመሆናቸው ነው።