عن ابن مسعود رضي الله عنه قال: قال النبي صلى الله عليه وسلم:
«الْجَنَّةُ أَقْرَبُ إِلَى أَحَدِكُمْ مِنْ شِرَاكِ نَعْلِهِ، وَالنَّارُ مِثْلُ ذَلِكَ».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ኢብኑ መስዑድ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዲህ ማለቱ ተላልፏል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡
"ጀነት ወደ እያንዳንዳችሁ ከጫማው ማሰሪያ የበለጠ ቅርብ ናት። እሳትም እንደዚሁ።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ ለሰው ልጅ ጀነትም ይሁን ጀሀነም በእግሩ ላይ እንዳለው የጫማው ማሰሪያ ቅርብ መሆናቸውን ተናገሩ። ምክንያቱም (ሳያስበው) አሏህን የሚያስደስት የሆነን መልካም ስራ ይሰራና በዛ ሰበብ ጀነት ይገባል። ወይም መጥፎ ስራ ይሰራና ጀሀነም ለመግባት ሰበብ ይሆንበታል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ቢያንስም መልካም ስራ ላይ መበርታት፤ ቢያንስም ከክፋት መጠንቀቅ እንደሚገባ፤
  2. ሙስሊም በህይወቱ በራሱ ሁኔታ ሳይሸወድ ሁሌም በተስፋና በስጋት መካከል ሊሆን እና እውነት ላይ እንዲያፀናውም ጥራት የተገባው አሏህን ሊማፀን የግድ እንደሚገባው እንረዳለን።