عن ابن مسعود رضي الله عنه قال: قال النبي صلى الله عليه وسلم:
«الْجَنَّةُ أَقْرَبُ إِلَى أَحَدِكُمْ مِنْ شِرَاكِ نَعْلِهِ، وَالنَّارُ مِثْلُ ذَلِكَ».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 6488]
المزيــد ...

ከኢብኑ መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንደተላለፈው እንዲህ ብሏል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፡
"ጀነት ወደ እያንዳንዳችሁ ከጫማው ማሰሪያ የበለጠ ቅርብ ናት። እሳትም እንደዚሁ።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 6488]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለሰው ልጅ ጀነትም ይሁን ጀሀነም በእግሩ ላይ እንዳለው የጫማው ማሰሪያ ቅርብ መሆናቸውን ተናገሩ። ምክንያቱም (ሳያስበው) አሏህን የሚያስደስት የሆነን መልካም ስራ ይሰራና በዛ ሰበብ ጀነት ይገባል። ወይም መጥፎ ስራ ይሰራና ጀሀነም ለመግባት ሰበብ ይሆንበታል።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ትንሽ ቢሆንም መልካም ስራ ላይ መበርታትና ትንሽ ቢሆንም ከክፋት መጠንቀቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
  2. ሙስሊም በህይወቱ በራሱ ሁኔታ ሳይሸወድ ሁሌም በተስፋና በስጋት መካከል ሊሆን እና እውነት ላይ እንዲያፀናውም ጥራት የተገባው አሏህን ሊማፀን የግድ እንደሚገባው እንረዳለን።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (67)