عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«الدُّنْيَا سِجْنُ الْمُؤْمِنِ وَجَنَّةُ الْكَافِرِ».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2956]
المزيــد ...
ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦
"ዱንያ ለአማኞች እስር ቤት ለከሃዲዎች ጀነት ናት።"»
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2956]
ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - አማኝ የሆነ ሰው በዱንያ ትእዛዛትን በመፈፀምና ክልከላን በመራቅ በኩል ሸሪዓዊ በሆኑ ሃላፊነቶች ስለታሰረ የዱንያ ህይወት ለአማኝ እስር ቤት እንደሆነች እና ከዚህም ሲሞት አላህ ለርሱ ወዳዘጋጀለት ዘውታሪ ፀጋ ተሸጋግሮ እንደሚያርፍ ተናገሩ። ከሃዲ የሆነ ሰው ደግሞ ነፍሱ የፈለገችውን ሁሉና ዝንባሌው የመራውን ሁሉ ስለሚሰራ ዱንያ ለከሃዲ ጀነት መሆኗንና ሲሞትም አላህ የትንሳኤ ቀን ወዳዘጋጀለት ዘውታሪ ቅጣት ይሸጋገራል ብለው ተናገሩ።