+ -

عَنْ أَبِي قَتَادَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«الرُّؤْيَا الصَّالِحَةُ مِنَ اللَّهِ، وَالحُلُمُ مِنَ الشَّيْطَانِ، فَإِذَا حَلَمَ أَحَدُكُمْ حُلُمًا يَخَافُهُ فَلْيَبْصُقْ عَنْ يَسَارِهِ، وَلْيَتَعَوَّذْ بِاللَّهِ مِنْ شَرِّهَا، فَإِنَّهَا لاَ تَضُرُّهُ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 3292]
المزيــد ...

ከአቡ ቀታዳህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"መልካም ህልም ከአላህ ነው። መጥፎ ህልም ከሸይጧን ነው። አንዳችሁ የሚፈራውን መጥፎ ህልም የተመለከተ ጊዜ ወደ ግራው ይትፋ፤ ከህልሙ ክፋትም በአላህ ይጠበቅ። ያኔ እርሷም አትጎዳውም።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 3292]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በእንቅልፍ የሚያስደስት መልካም ህልም መመልከት ከአላህ እንደሆነና የሚጠላውንና የሚያሳዝነውን ቅብዥር መመልከት ደግሞ ከሸይጧን እንደሆነ ተናገሩ።
የሚጠላውን ህልም የተመለከተ ሰው ወደ ግራው አቅጣጫ ይትፋ፤ ከህልሙ ክፋትም በአላህ ይጠበቅ። ቅብዥሩን ተከትሎ ከሚመጡ ጎጂዎች ሰላም ለመሆን የተጠቀሰውን ማድረግ አላህ ሰበብ ስላደረገው እርሷ አትጎዳውም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. "ሩእያ" እና "ሑልም" የሚሉት ሁለት የዐረብኛ ቃላቶች የተኛ ሰው በእንቅልፉ የሚያየውን የሚገልፁ ቃላቶች ሲሆኑ ነገር ግን "ሩእያ" የሚለው ቃል በብዛት በህልሙ ለሚያየው መልካምና ጥሩ ነገር ሲውል፤ "ሑልም" የሚለው ቃል ደግሞ በብዛት በህልሙ ለሚያየው መጥፎና አስቀያሚ ነገር ይውላል። እያንዳንዱ ቃል ግን በሌላኛው ቦታ ላይ ሊውል ይችላል።
  2. የህልም ክፍሎች: 1 - መልካም ህልም: ይህም የሚያያት ወይም የሚታይለት የሆነ እውነተኛና ከአላህ የሆነ ብስራት ነው። 2 - ቅዥት: ይህም ሰውዬው ነቅቶ ባለበት በውስጡ ሲያብሰለስለው የነበረውን ተኝቶ ማየቱ ነው። 3 - የሸይጧን ማሳዘኛና ማስፈራሪያ የሆነ፣ የአደምን ልጅ ለማስፈራራት ከርሱ የሆኑ ማስደንገጫዎች የሆነ ቅብዥር ነው።
  3. መልካም ህልም ባየ ሰው ዙሪያ የተጠቀሱት ነጥቦች ሶስት ናቸው: አላህን ማመስገን፣ በህልሙ መደሰትና ስላየው ህልም መናገር ነው። ነገር ግን የሚናገረው ለሚጠላው ሳይሆን ለሚወደው ሰው ብቻ ነው።
  4. የሚጠላውን ህልም ባየ ሰው አደብ ዙሪያ የተጠቀሱት ነጥቦች አምስት ነገሮች ናቸው: ከህልሙ ክፋትና ከሸይጧን ክፋት በአላህ መጠበቅ፤ ከእንቅልፉ በሚነቃ ጊዜ ወደ ግራው ዞሮ ሶስት ጊዜ መትፋት፤ ከመሰረቱ ለአንድም ሰው አለመንገር፤ ወደ መኝታው መመለስ ከፈለገ የነበረበትን ጎን ቀይሮ መዞር ነው። ይህን ካደረገ ህልሙም አይጎዳውም።