عن جابر بن عبد الله رضي الله عنهما قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول:
«مَنْ لَقِيَ اللهَ لَا يُشْرِكُ بِهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ، وَمَنْ لَقِيَهُ يُشْرِكُ بِهِ دَخَلَ النَّارَ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ጃቢር ቢን ዓብደሏህ ረዲየሏሁ ዓንሁማ እንዲህ ማለታቸው ተላልፏል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፡
"በአሏህ ሳያጋራ አሏህን የተገናኘ ጀነት ገብቷል፤ እያጋራበት አሏህን የተገናኘ ደግሞ እሳት ገብቷል።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ በአሏህ ላይ አንዳችም ሳያጋራ የሞተ በተወሰነ ወንጀሉ ተቀጥቶም ቢሆን መመለሻው ወደ ጀነት መሆኑን፤ በአሏህ ላይ አንዳችም አጋርቶ የሞተ ደግሞ ጀሀነም መዘውተሪያው መሆኑን ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ተውሒድ ያለው ትሩፋት፤ በእሳት ውስጥ ከመዘውተር ለመዳንም ሰበብ መሆኑን፤
  2. የሰው ልጅ ከጀሀነምም ይሁን ከጀነት ጋር ያለው ቅርበት፤ በመካከላቸው ያለውም ሞት ብቻ መሆኑን፤
  3. ከጥቂትም ይሁን ከብዙ ሽርክ መጠንቀቅ እንደሚገባ፤ ምክንያቱም ከጀሀነም እሳት መዳን የሚቻለው ያንን በመራቅ ስለሆነ፤
  4. ስራዎች ዋጋ የሚሰጣቸው በፍፃሜያቸው መሆኑን እንረዳለን።