عن ابْنِ عُمَرَ رضي الله عنهما أنه سَمِعَ رَجُلًا يَقُولُ: لَا وَالْكَعْبَةِ، فَقَالَ ابْنُ عُمَرَ: لَا يُحْلَفُ بِغَيْرِ اللَّهِ، فَإِنِّي سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«مَنْ حَلَفَ بِغَيْرِ اللهِ فَقَدْ كَفَرَ أَوْ أَشْرَكَ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي وأحمد]
المزيــد ...

ከኢብኑ ዑመር ረዲየሏሁ ዓንሁማ እንደተላለፈው የሆነ ሰው እንዲህ ሲል ሰሙ፡ "በካዕባ ይሁንብኝ በፍፁም!" ኢብኑ ዑመርም ረዲየሏሁ ዓንሁማ እንዲሁ አሉ፡ "ከአሏህ ውጭ ባለ አካል አይማልም! ምክንያቱም ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁና
'ከአሏህ ውጭ ባለ አካል የማለ ከፍሯል ወይም አጋርቷል።'"

Sahih/Authentic. - [At-Tirmidhi]

ትንታኔ

በአሏህ ወይም በስምና ባህርያቱ ካልሆነ በቀር ከዛ ውጪ በሆነ መሀላ የማለ ሰው በአላህ ክዷል ወይም አጋርቷል እያሉን ነው። ምክንያቱም በአንድ አካል መማል እሱን ማላቃችንን ያስፈርዳል ፤ በእውነቱ ልቅና ደግሞ የሚገባው ለአሏህ ብቻ ነው። ስለዚህም በሱ ወይም ከስምና ባህሪዎቹ መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር አይማልም። ይህ መሀላ ከትንሹ ሽርክ የሚመደብ ነው። ይሁን እንጂ የማለው ሰው የማለበትን አካል እንደ አሏህ ወይም ከዛም በላይ አልቆት ከሆነ ግን መሃላው ትልቁ ሽርክ ይሆናል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በመሀላ ማላቅ ጥራት የተገባው የአሏህ ሓቅ ነው። በመሆኑም በአላህ ፣ በስምና ባህርያቱ ካልሆነ በቀር በሌላ አይማልም።
  2. ሶሓቦች በመልካም ለማዘዝ እና ከመጥፎ ለመከልከል የነበራቸውን ጉጉት ያሳያል፤ በተለይም ጥፋቱ ሽርክን ወይም ክህደትን የሚመለከት ሲሆን የበለጠ ጉጉት አላቸው።