عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الخُدْرِيَّ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ -وَكَانَ غَزَا مَعَ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ ثِنْتَيْ عَشْرَةَ غَزْوَةً- قَالَ: سَمِعْتُ أَرْبَعًا مِنَ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَأَعْجَبْنَنِي، قَالَ:
«لاَ تُسَافِرِ المَرْأَةُ مَسِيرَةَ يَوْمَيْنِ إِلَّا وَمَعَهَا زَوْجُهَا أَوْ ذُو مَحْرَمٍ، وَلاَ صَوْمَ فِي يَوْمَيْنِ: الفِطْرِ وَالأَضْحَى، وَلاَ صَلاَةَ بَعْدَ الصُّبْحِ حَتَّى تَطْلُعَ الشَّمْسُ، وَلاَ بَعْدَ العَصْرِ حَتَّى تَغْرُبَ، وَلاَ تُشَدُّ الرِّحَالُ إِلَّا إِلَى ثَلاَثَةِ مَسَاجِدَ: مَسْجِدِ الحَرَامِ، وَمَسْجِدِ الأَقْصَى، وَمَسْجِدِي هَذَا».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንደተላለፈው ‐ ከነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጋር አስራ ሁለት ዘመቻዎችን ዘምቷል። ‐ እንዲህ አለ: "አራት ነገሮችን ከነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሰምቼ አስደንቀውኛል። እንዲህ ብለዋል:
'ሴት ልጅ ከርሷ ጋር ባሏ ወይም ዘመዷ ከሌሉ በቀር ሁለት ቀን የሚያስኬድ መንገድን አትጓዝ። ሁለት ቀናት ላይ መፆም የለም፤ ዒደል ፊጥርና አድሓ። ከሱብሒ በኋላ ፀሀይ እስክትወጣ ድረስ ሶላት የለም፤ ከዐስር በኋላም ፀሀይ እስክትገባ ድረስም ሶላት የለም። ወደ ሶስት መስጂዶች ካልሆነ በቀርም ጓዝን ሸክፎ አይኬድም: ወደ መስጂደል ሐራም፣ ወደ መስጂደል አቅሷና ወደዚህ መስጂዴ።'"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከአራት ጉዳዮች ከለከሉ።
የመጀመሪያው: ሴት ልጅን ያለባሏ ወይም ያለ አንድ ዘመዷ ሁለት ቀን የሚያስኬድ መንገድ ከመጓዝ መከልከል ነው። ዘመዷ የተባሉትም እንደ ልጅ፣ አባት፣ የወንድም ልጅ፣ የእህት ልጅ፣ አጎትና የመሳሰሉት ያሉ ለዘላለም በነርሱ ላይ ለጋብቻ እርም የተደረገችባቸው ቅርብ ዘመዶቿ ናቸው።
ሁለተኛው: የዒደል ፊጥርና የዒደል አድሓ ቀንን የመፆም ክልክልነት ነው። በነዚህ ቀናቶች ላይ አንድ ሙስሊም ለስለትም ወይም ለበጎ ፍቃደኝነትም ወይም ለማካካሻ ብሎም መፆሙ ክልክል ነው።
ሶስተኛው: ከዐስር ሶላት በኋላ ፀሀይ እስክትገባ ድረስና ጎህ ከቀደደ በኋላ ፀሀይ እስክትወጣ ድረስ ሱና ሶላትን ከመስገድ መከልከሉ ነው።
አራተኛው: ከነዚህ ሶስት መስጂዶች በቀር ወደ ማንኛውም ስፍራ ወደርሱ የመጓዝን ብልጫ አስቦ፣ በመጓዝ ምክንያትም ምንዳ ይነባበራል ብሎ በማመን መጓዝ መከልከላቸው ነው። ከነዚህ ሶስት መስጂዶች በቀርም በውስጧ ለመስገድ በሚል ጓዝ ተሸክፎ አይኬድም። ከነዚህ ሶስት መስጊዶች በቀርም ምንዳ አይነባበርምና። እነሱም: መስጂደል ሐራም፣ የነቢዩ መስጂድና መስጂደል አቅሷ ናቸው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሴት ልጅ ያለ ቅርብ ዘመዷ መጓዟ አለመፈቀዱን እንረዳለን።
  2. ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) "ባሏ ወይም ቅርብ ዘመዷ" ስላሉ፤ ሴት ልጅ ለሴት ልጅ ጉዞ ላይ መሕረም አትሆንም።
  3. ጉዞ ተብሎ የሚጠራን ሁሉ ሴት ልጅ ከባሏ ጋር ወይም ቅርብ ዘመዷ ጋር ካልሆነች በቀር መጓዟ ትከለከላለች። በዚህ ሐዲሥ የተጠቀሰውም ከጠያቂውና ከስፍራው መጠን አንፃር ነው።
  4. የሴት ልጅ መሕረም የሚባለው ባሏ ወይም እንደ አባት፣ ልጅ፣ አጎት የመሰሉ በቅርብ ዝምድና ምክንያት ከነርሱ ጋር መጋባትን ለዘላልም እርም የተደረገባት አካላቶች፤ ወይም እንደጥቢ አባቷ፣ የጥቢ አጎቷ ይመስል በጥቢ ምክንያት ከነርሱ ጋር ለዘላለም መጋባትን እርም የተደረገባት አካላቶች፤ ወይም እንደባል አባት የመሰሉ በአማችነት ምክንያት ከነርሱ ጋር መጋባትን እርም የተደረገባት አካላት ናቸው። "መሕረም" የተባለው ሙስሊም፣ አቅመ አዳም የደረሰ፣ ጤነኛና ታማኝ መሆን ይገባዋል። ከመሕረሙ የተፈለገው ነገር ሴትን መጠበቅ ከለላ መሆንና የሚያስፈልጋትን ማሟላት ነውና።
  5. ኢስላማዊ ሸሪዓ በሴት ጉዳይ ትኩረት መስጠቱን፣ መጠበቁንና ከለላ መሆኑን እንረዳለን።
  6. ልቅ የሆኑ (በጊዜ ያልተገደቡ) ሱና ሶላቶች ከፈጅርና ዐስር ሶላት በኋላ ተቀባይነት እንደሌላቸው እንረዳለን። ከዚህ ውስጥ ግን ያመለጡ ግዴታ ሶላቶችና እንደተሒየተል መስጂድ ያሉት ምክንያት ያላቸው ሶላቶች ተለይተው ይወጣሉ።
  7. ፀሀይ ከወጣች በኋላ በቀጥታ ሶላት መስገድ ክልክል ነው። ይልቁንም የግድ ከአስር ደቂቃ እስከ ሩብ ሰአት ያክል ቆይቶ የጦር ርዝመት ያክል ከፍ እስክትል ድረስ መጠበቅ ይገባል።
  8. የዐስር ወቅት ፀሀይ እስክትገባ ድረስ ይረዝማል።
  9. ከዚህ ሐዲሥ ወደ ሶስቱ መስጊድ ጓዝ ሸክፈን መጓዝ እንደሚፈቀድ እንረዳለን።
  10. የሶስቱ መስጂዶችን ትሩፋትና ከሌሎች መስጂዶች የተለዩ መሆናቸውን እንረዳለን።
  11. የነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ቀብር እንኳ ቢሆን ቀብሮችን ለመዘየር መጓዝ እንደማይፈቀድ እንረዳለን። መዲና ውስጥ ላለ ወይም ለሸሪዓዊና ለተፈቀደ ዓላማ ለመጣ ሰው ግን መዘየሩ ይፈቀድለታል።
ተጨማሪ