عن عبد الله بن عمرو رضي الله عنهما أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«الدُّنْيَا مَتَاعٌ، وَخَيْرُ مَتَاعِ الدُّنْيَا الْمَرْأَةُ الصَّالِحَةُ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን ዐምር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
"ዱንያ መጣቀሚያ ናት። ከዱንያ መጣቀሚያዎች ምርጡ መልካም ሚስት ናት።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዱንያም ውስጧ ያሉ ነገሮችም በሙሉ ጊዜያዊ መጠቀሚያዎች ሆነው ከዚያም የሚጠፉ መሆናቸውን፤ በላጩ መጣቀሚያም ሲያያት የምታስደስተው፣ ሲያዛት የምትታዘዘው፣ ሲርቅ ነፍሷንና ንብረቱን የምትጠብቅ መልካም ሚስት መሆኗን ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህ ለባሮቹ ፍቁድ ባደረጋቸው የዱንያ መልካም ነገሮች ላይ ያለማባከንና ያለመኩራራት መጠቀም መፈቀዱን ፤
  2. ባልን በጌታው አምልኮ ላይ ስለምታግዝ መልካም ሚስት በመምረጥ ላይ መነሳሳቱን ፤
  3. ከዱንያ መጣቀሚያዎች ሁሉ ምርጡ አላህን በማምለክ ላይ የሆነ ወይም አላህን በማምለክ ላይ አጋዥ የሆኑ ነገር መሆኑን እንረዳለን።