عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا:
أَنَّ رَجُلًا سَأَلَ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: أَيُّ الإِسْلاَمِ خَيْرٌ؟ قَالَ: «تُطْعِمُ الطَّعَامَ، وَتَقْرَأُ السَّلاَمَ عَلَى مَنْ عَرَفْتَ وَمَنْ لَمْ تَعْرِفْ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን ዐምር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:-
"አንድ ሰውዬ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) 'ማንኛው የኢስላም ክፍል ነው ምርጡ?' ብሎ ጠየቀ። እርሳቸውም 'ምግብ መመገብህ፣ ሰላምታን ባወቅከውም ባላወቅከውም ሰው ላይ ማቅረብህ ነው።' ብለው መለሱለት።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ማንኛው የኢስላም ክፍል ነው በላጩ? ተብለው ተጠየቁ። እርሳቸውም ሁለት ነገሮችን ጠቀሱ።
የመጀመሪያው: ድሃዎችን ማብላትን ማብዛት ነው። እዚህ ውስጥም ሶደቃ፣ ስጦታ፣ ግብዣ፣ የሰርግ ድግስ ይገባሉ። የማብላቱ በላጭነትም በረሃብና ኑሮ በተወደደበት ወቅት የጠነከረ ይሆናል።
ሁለተኛው: አወቅከውም አላወቅከውም በሁሉም ሙስሊም ላይ ሰላምታን ማቅረብ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሶሐቦች በዱንያም ሆነ በመጨረሻው ዓለም የሚጠቅመምን ጉዳይ ለማወቅ ያላቸውን ጉጉት እንረዳለን።
  2. ሰላምታ ማቅረብና ምግብ ማብላት ሰዎች በሁሉም ወቅት የሚፈልጉት ስለሆነና በላጭ ስራ ከመሆኑ አንፃርበ ኢስላም ውስጥ ትልቅ ደረጃ ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል እንደሆኑ እንረዳለን።
  3. በነዚህ ሁለት ጉዳዮች ንግግራዊም ተግባራዊም በጎነት ይሰበሰባሉ። ይህም የተሟላው በጎነት ነው።
  4. እነዚህ ጉዳዮች ሙስሊሞች በመካከላቸው ሊኖራቸው ከሚገባው መስተጋብር ጋር የተያያዘ ሲሆን ሌላ ቦታ ደግሞ አንድ ባሪያ ከጌታው ጋር ሊኖረው ስለሚገባ መስተጋብር የሚገልፁ ጉዳዮች አሉ።
  5. በሰላምታ መጀመር በሙስሊሞች መካከል ብቻ የተገደበ ሲሆን ካፊር በሰላምታ አይጀመርም።