عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
«لَيْسَ الشَّدِيدُ بِالصُّرَعَةِ، إِنَّمَا الشَّدِيدُ الَّذِي يَمْلِكُ نَفْسَهُ عِنْدَ الْغَضَبِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና-እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡
"ብርቱ የሚባለው ታግሎ ያሸነፈ ሳይሆን በቁጣ ወቅት እራሱን የተቆጣጠረ ነው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ትክክለኛ ሀይል አካላዊ ሀይል ወይም ጉልበተኞችን የሚጥል ሳይሆን ብርቱና ሀይለኛ የሚባለው ቁጣው በሚበረታ ወቅት ነፍሱን የታገለና ያሸነፋት መሆኑን ገለፁ። ምክንያቱም ይህ ሰው ነፍሱን የመቆጣጠርና ሰይጣንን የማሸነፍ አቅም እንዳለው ይጠቁማልና።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የቻይነትና ነፍስን በቁጣ ወቅት የመቆጣጠር ትሩፋትን እንረዳለን። ይህ ኢስላም ያነሳሳበት ከሆኑ መልካም ስራዎች መካከል አንዱ ነውና።
  2. ነፍስን በቁጣ ወቅት መታገል ጠላትን ከመታገልም የበለጠ ከባድ መሆኑን እንረዳለን።
  3. ጃሂሊዮች ለሀይለኝነት የሰጡትን ትርጓሜ ኢስላም ወደ ክቡር መገለጫ ስነ ምግባር መለወጡን እንረዳለን። ከሰዎች ሁሉ እጅግ ብርቱ የነፍሱን ልጓም የተቆጣጠረ ነውና።
  4. በግለሰብም ደረጃ ይሁን በማህበረሰብ ደረጃ ጉዳት ከማስከተሉ አኳያ ከቁጣ መራቅ እንደሚገባ እንረዳለን።