____
[] - []
المزيــد ...
ከአቡ መስዑድ ዑቅባ ቢን ዓምር አልአንሷሪይ አልበድሪይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: «የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል:
"ሰዎች ከቀደምት ነቢያት ካገኟቸው ቃላት መካከል ካላፈርክ የፈለግከውን ስራ! የሚለው አንዱ ነው።"»
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [الأربعون النووية - 20]
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ወደዚህ ኡመት መጀመሪያ እስኪደርስ ድረስ ከቀደምት ነቢያት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲወራረሱትና በመካከላቸው ሲቀባበሉት ከነበሩ አደራዎች መካከል ልትሰራው የምትፈልገውን ስራ ተመልከት! ማድረጉ የማያሳፍር ስራ ከሆነ ስራው! የሚያሳፍር ስራ ከሆነ ተወው! የሚለው ይገኝበታል። ፀያፍን ከመስራት የሚከለክለው ሀፍረት ነው። ሀፍረት የሌለው ሰው በየትኛውም ፀያፍና ውግዝ ተግባር ውስጥ ይዘፈቃል።