عن أنس بن مالك رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«إِنَّ اللهَ لَيَرْضَى عَنِ الْعَبْدِ أَنْ يَأْكُلَ الْأَكْلَةَ فَيَحْمَدَهُ عَلَيْهَا، أَوْ يَشْرَبَ الشَّرْبَةَ فَيَحْمَدَهُ عَلَيْهَا».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ ብሏል: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
'አላህ ባሪያው ምግብን በልቶ እንዲያመሰግነው ወይም መጠጥን ጠጥቶ እንዲያመሰግነው ይወዳል።'"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

አንድ ባሪያ ጌታውን በቸረውና ባጣቀመው ፀጋዎቹ ምክንያት ማመስገኑ የአላህ ውዴታን ከሚያገኝባቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ ስለሆነ ምግብ በልቶም "አልሐምዱሊላህ" ማለት ፤ የሚጠጣም ጠጥቶ "አልሐምዱሊላህ" ማለት እንደሚገባው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህ ሲሳይን ችሮን በምስጋናችን በመደሰቱ የርሱን ችሮታ እንረዳለን።
  2. የአላህ ውዴታ ከመብላትና መጠጣት በኋላ ማመስገንን በመሰለ ትንሽ ምክንያት እንኳ እንደሚገኝ እንረዳለን።
  3. ከምግብና መጠጥ ስነስርአቶች መካከል ከበሉና ከጠጡ በኋላ አላህን ማመስገን አንዱ ነው።