عن أنس بن مالك رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«إِنَّ اللهَ لَيَرْضَى عَنِ الْعَبْدِ أَنْ يَأْكُلَ الْأَكْلَةَ فَيَحْمَدَهُ عَلَيْهَا، أَوْ يَشْرَبَ الشَّرْبَةَ فَيَحْمَدَهُ عَلَيْهَا».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2734]
المزيــد ...

ከአነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ ብሏል: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
'አላህ ባሪያው ምግብን በልቶ እንዲያመሰግነው ወይም መጠጥን ጠጥቶ እንዲያመሰግነው ይወዳል።'"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2734]

ትንታኔ

አንድ ባሪያ ጌታውን በቸረውና ባጣቀመው ፀጋዎቹ ምክንያት ማመስገኑ የአላህ ውዴታን ከሚያገኝባቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ ስለሆነ ምግብ በልቶም "አልሐምዱሊላህ" ማለት ፤ የሚጠጣም ጠጥቶ "አልሐምዱሊላህ" ማለት እንደሚገባው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ገለፁ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህ ሲሳይን ችሮን በምስጋናችን መደሰቱ የርሱን ችሮታ እንረዳለን።
  2. የአላህ ውዴታ ከመብላትና መጠጣት በኋላ ማመስገንን በመሰለ ትንሽ ምክንያት እንኳ እንደሚገኝ እንረዳለን።
  3. ከምግብና መጠጥ ስነስርአቶች መካከል ከበሉና ከጠጡ በኋላ አላህን ማመስገን አንዱ ነው።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (63)