عَنْ عَائِشَةَ أُمِّ المُؤْمِنين رضي الله عنها زَوْجِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«يَا عَائِشَةُ إِنَّ اللهَ رَفِيقٌ يُحِبُّ الرِّفْقَ، وَيُعْطِي عَلَى الرِّفْقِ مَا لَا يُعْطِي عَلَى الْعُنْفِ، وَمَا لَا يُعْطِي عَلَى مَا سِوَاهُ».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2593]
المزيــد ...
የነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ባለቤት ከሆነችው ከአማኞች እናት ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ አሉ፦
"ዓኢሻ ሆይ! አላህ ርህሩህ ነው። ለስላሳነትንም ይወዳል። አላህ በግትርነት ላይና ከልስላሴ ውጪ ባሉ መስተጋብሮች ላይ የማይሰጠውንም በልስላሴ ይሰጣል።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2593]
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ለአማኞች እናት ለሆነችው ለዓኢሻ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- በእዝነት ላይ አነሳሷት። አላህ ለባሮቹ ርህሩህና ለስላሳ ነው። ለነርሱ ገርን ይፈልግላቸዋል። ለነርሱ ችግርን አይፈልግም። ከአቅማቸው በላይም አያስገድዳቸውም። የአላህ ባሪያ የሆነም ሰው ገራገር ማንነትን መላበሱንና ገርን መውሰዱን አላህ ይወድለታል። ልበ ደረቅና ስነምግባረ ብልሹ መሆንም የለበትም። አላህ በዱንያ ውስጥ እዝነትና ገራገርነትን ለተላበሰ ሰው ባማረ ሙገሳ ያወሳዋል፣ ፍላጎቱን ያሟላለታል፣ ግቡንም ያሳካለታል። በመጪው ዓለም ደግሞ ትልቅ ምንዳን ይሰጠዋል። ይህም ግትርነት፣ ድርቅናና ሀይለኝነትን ለተላበሰ ሰው ከሚሰጠው የበዛ ምንዳ ነው። ለስላሳነትን መላበስ ሌሎች ባህሪያትን መላበስ የማያመጡትን ጥቅም ይዞ ይመጣል።