عن عثمان رضي الله عنه عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«خَيْرُكُمْ مَنْ تَعَلَّمَ الْقُرْآنَ وَعَلَّمَهُ».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 5027]
المزيــد ...

ከዑስማን -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
"ከናንተ መካከል በላጩ ቁርአንን ተምሮ ያስተማረ ሰው ነው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 5027]

ማብራሪያ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከሙስሊሞች መካከል በላጩና አላህ ዘንድ ከፍተኛ ደረጃ ያለው ቁርአን ማንበብን፣ መሸምደድን፣ ማሳመርን፣ መገንዘብንና ማብራራትን የተማረና እርሱ ዘንድ ያለውን የቁርአን እውቀት ከመተግበሩም ጋር ለሌላው ያስተማረ መሆኑን ተናገሩ።

ከሐዲሡ የሚቀሰሙ ቁምነገሮች

  1. የቁርአን ልቅና መገለፁ። ቁርአን የአላህ ቃል ስለሆነ ምርጡ ቃል ነው።
  2. ምርጥ ተማሪ ማለት ሌላውንም የሚያስተምር እንጂ በነፍሱ ላይ የሚገደብ አይደለም።
  3. ቁርአንን መማርና ማስተማሩ ማንበቡንም፣ ትርጉሙንም ህግጋቱንም ያካትታል።
ትርጉሞችን አሳይ
ቋንቋ: الإنجليزية الأوردية الإسبانية ተጨማሪ (64)
ተጨማሪ