عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ:
لَمَّا نَزَلَتْ: {إِنَّا فَتَحْنَا لَكَ فَتْحًا مُبِينًا لِيَغْفِرَ لَكَ اللهُ} إِلَى قَوْلِهِ {فَوْزًا عَظِيمًا} [الفتح: ١-٥] مَرْجِعَهُ مِنَ الْحُدَيْبِيَةِ، وَهُمْ يُخَالِطُهُمُ الْحُزْنُ وَالْكَآبَةُ، وَقَدْ نَحَرَ الْهَدْيَ بِالْحُدَيْبِيَةِ، فَقَالَ: «لَقَدْ أُنْزِلَتْ عَلَيَّ آيَةٌ هِيَ أَحَبُّ إِلَيَّ مِنَ الدُّنْيَا جَمِيعًا».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 1786]
المزيــد ...
ከአነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦
«ሐዘንና ትካዜ ወርሯቸው፣ ቁርባኑንም (ሀድዩን) አርደው ከሑደይቢያ እየተመለሱ ሳሉና {እኛ ላንተ ግልፅ የሆነን መክፈት ከፈትንልህ። አላህ ካንተ ሊምር} ከሚለው {ታላቅ ማግኘት ነው።} እስከሚለው ድረስ [አልፈትሕ: 1 - 5] ያሉት አንቀፆች በወረዱ ጊዜ ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ አሉ: "ከዱንያ ባጠቃላይ በልጣ እኔ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነች አንቀፅ በኔ ላይ ወረደች።"»
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1786]
አነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ ሲሉ ተናገሩ: በአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ይህ የአላህ ቃል የወረደ ጊዜ: {(1) እኛ ላንተ ግልፅ የሆነን መክፈት ከፈትንልህ። (2) አላህ ከኀጢአትህ ያለፈውንና የሚመጣውን ላንተ ሊምር ጸጋውንም ባንተ ላይ ሊሞላ ቀጥተኛውንም መንገድ ሊመራህ (ከፈተልህ)። (3) አላህ ብርቱን እርዳታ ሊረዳህም (ከፈተልህ)። (4) እርሱ ያ በምእመናን ልቦች ውስጥ ከእምነታቸው ጋር እምነትን ይጨምሩ ዘንድ እርጋታን ያወረደ ነው። ለአላህም የሰማያትና የምድር ሰራዊቶች አሉት። አላህም አዋቂ ጥበበኛ ነው። (5) ምእመናንንና ምእመናትን ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈስባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲሆኑ ሊያገባቸው ከነርሱም ሀጢአቶቻቸውን ሊያብስላቸው (በትግል አዘዛቸው)። ይህም ከአላህ ዘንድ የሆነ ታላቅ ማግኘት ነው።} [አልፈትሕ: 1-5] እነዚህ አንቀጾች የወረዱትም ሶሓቦች በሑደይቢያ ስምምነቱ መካሄድ ምክንያት ዑምራን ከማድረግ ክልከላ ተጥሎባቸው ሀድያቸውን (ቁርባናቸውን) በሑደይቢያ አርደው ስምምነቱ የሙስሊሞችን ጥቅም ያስጠበቀ አይደለም በሚል ሀዘንና ትካዜ ወርሯቸው ከዛ በሚመለሱበት ወቅት ነበር። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ አሉ: እኔ ዘንድ ከዱንያ ባጠቃላይ ተወዳጅ የሆነች አንቀፅ በኔ ላይ ወረደች። ቀጥለውም አነበቧት።