+ -

عَنْ أُمِّ سَلَمَةَ أُمِّ المؤْمنينَ رَضيَ اللهُ عنها أَنَّهَا قَالَتْ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ:
«مَا مِنْ مُسْلِمٍ تُصِيبُهُ مُصِيبَةٌ فَيَقُولُ مَا أَمَرَهُ اللهُ: {إِنَّا لِلهِ وَإِنَّا إِلَيْهِ رَاجِعُونَ} [البقرة: 156]، اللَّهُمَّ أْجُرْنِي فِي مُصِيبَتِي، وَأَخْلِفْ لِي خَيْرًا مِنْهَا، إِلَّا أَخْلَفَ اللهُ لَهُ خَيْرًا مِنْهَا»، قَالَتْ: فَلَمَّا مَاتَ أَبُو سَلَمَةَ قُلْتُ: أَيُّ الْمُسْلِمِينَ خَيْرٌ مِنْ أَبِي سَلَمَةَ؟ أَوَّلُ بَيْتٍ هَاجَرَ إِلَى رَسُولِ اللهِ صلى الله عليه وسلم، ثُمَّ إِنِّي قُلْتُهَا، فَأَخْلَفَ اللهُ لِي رَسُولَ اللهِ صلى الله عليه وسلم.

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 918]
المزيــد ...

ከአማኞች እናት ከኡሙ ሰለማ ረዺየሏሁ ዐንሃ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ:
"አንድም መከራ አጋጥሞት አላህ እንዳዘዘው ‹{ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን} [አልበቀራ:156] አልላሁመእጁርኒ ፊ ሙሲበቲ፣ ወአኽሊፍ ሊ ኸይረን ሚንሃ› የሚል ሙስሊም የለም አላህ ከዛ የተሻለ ነገር ቢተካለት እንጂ።"» ኡሙ ሰለማ እንዲህ አለች: "አቡ ሰለማ የሞተ ጊዜ እንዲህ አልኩኝ: ከአቡ ሰለማ የተሻለ ሙስሊም ከቶ ማን አለና?! ወደ አላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በቅድሚያ የተሰደደ ቤተሰብ ነው። ከዚያም ይህንን ዱዓ አልኩኝ። አላህም ለኔ የአላህን መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ተካልኝ።" ትርጉሙም ({እኛ ለአላህ ነን እኛም ወደርሱ ተመላሾች ነን።} [አልበቀራ:156] አላህ ሆይ በመከራዬ ምንዳን ስጠኝ። ከደረሰበኝ መከራ የተሻለንም ተካልኝ።) ማለት ነው።

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 918]

ትንታኔ

የአማኞች እናት ኡሙ ሰለማ ረዲየሏሁ ዐንሃ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - አንድ ጊዜ ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሲሉ እንደሰማች አወሳች: አንድም መከራ የሚደርስበትና አላህ ለርሱ የመረጠለትን ይህንን ውዳሴ የሚል ሙስሊም የለም: {ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን} [አልበቀራ:156] ትርጉሙም {እኛ ለአላህ ነን እኛም ወደርሱ ተመላሾች ነን።} (አላሁመእጁርኒ) አላህ ሆይ! በደረሰበኝ መከራ የትእግስቴን ምንዳ ስጠኝ! (ፊ ሙሲበቲ) (ወአኽሊፍ ሊ ኸይረን ሚንሃ) ከርሱ የተሻለንም ለኔ ተካልኝ አይልም አላህ ለርሱ ከደረሰበት መከራ የተሻለን ቢለውጥለት እንጂ። ኡሙ ሰለማ እንዲህ አለች: አቡ ሰለማ የሞተ ጊዜ እንዲህ አልኩኝ: "ከአቡ ሰለማ የተሻለ ሙስሊም ከቶ ማን አለ? ወደ አላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - በቅድሚያ የተሰደደ ቤተሰብ ነው። ከዚያም ግን አላህ አግዞኝ ይህንን ውዳሴ ተናገርኩት። አላህም ለኔ ከአቡ ሰለማ የተሻሉትን የአላህን መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ተካልኝ።"

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. መከራ በሚያጋጥም ወቅት ባለመበሰጫጨትና ትእግስት በማድረግ መታዘዙን እንረዳለን።
  2. መከራ በሚያጋጥም ወቅት አላህ ዘንድ ምትኩ ስላለ ዱዓእ በማድረግ ወደ አላህ መዞር እንደሚገባ እንረዳለን።
  3. አንድ አማኝ የነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ትእዛዝ ጥበቡ ባይታየው እንኳ የርሳቸውን ትእዛዝ መፈፀም አስፈላጊነቱን እንረዳለን።
  4. የተሟላ መልካም የሚባለው አንድ አማኝ የነቢዩን ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ትእዛዝ ሲተገብር ነው።
ትርጉም: እንግሊዝኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ