عَنْ أَبِي الْجَعْدِ الضَّمْرِيِّ رَضيَ اللهُ عنهُ، وَكَانَتْ لَهُ صُحْبَةٌ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«مَنْ تَرَكَ ثَلَاثَ جُمَعٍ تَهَاوُنًا بِهَا طَبَعَ اللَّهُ عَلَى قَلْبِهِ».
[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي وابن ماجه وأحمد] - [سنن أبي داود: 1052]
المزيــد ...
ከአቢ ጀዕድ አድዶምሪይ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - (ከነቢዩ ሶሓቦች መካከልም አንዱ ነበር) እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል:
"ሶስት ጁመዓዎችን በመሳነፍ የተወ ሰው አላህ ልቡ ላይ ያሽግበታል።"
[ሶሒሕ ነው።] - - [ሱነን አቡዳውድ - 1052]
ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የጁሙዓን ሶላት ከመተው አስጠነቀቁ። ሶስት ጊዜ የጁመዓን ሶላቶች ያለምንም በቂ ምክንያት በመሳነፍና በመዘናጋት የተወ ሰው አላህ መልካም ነገር ወደርሱ እንዳይደርስ በመከልከል ቀልቡን ያሽገዋልም ከመልካም ነገር ይጋርደዋልም።