عن عبد الله بن عُمر وأبي هريرة رضي الله عنهما أنهما سمعا رسول الله صلى الله عليه وسلم، يقول على أعواد منبره:
«لَيَنْتَهِيَنَّ أَقْوَامٌ عَنْ وَدْعِهِمُ الْجُمُعَاتِ أَوْ لَيَخْتِمَنَّ اللهُ عَلَى قُلُوبِهِمْ، ثُمَّ لَيَكُونُنَّ مِنَ الْغَافِلِينَ».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 865]
المزيــد ...
ከዐብደላህ ቢን ዑመርና አቡ ሁረይራ ረዺየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: እነርሱ የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በሚንበራቸው እንጨት ላይ ሆነው እንዲህ ሲሉ ሰሙ:
"ሰዎች ጁመዓዎችን ከመተው ይከልከሉ! አለበለዚያ ግን አላህ በልቦቻቸው ላይ ያሽጋል። ከዚያም ከዝንጉዎች ይሆናሉ።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 865]
ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሚንበራቸው ላይ ሆነው ጁመዓን ያለምንም ተቀባይ ምክንያት በስንፍናና በማቃለል ከመተውና ከርሱ ወደኃላ ማለትን አስጠነቀቁ። ያለበለዚያ ግን አላህ በልቦቻቸው ላይ እንደሚያሽግና እንደሚሸፍን፤ በቀልባቸው ላይ እውነትን ከመከተል የሚያቅብ ግርዶሽ እንደሚያደርግና ከዚያም ከመልካም መንገዶች ከሚዘናጉትና ነፍሳቸውም ከአምልኮ ቸልተኛ ከሆኑት እንደምትሆን ተናገሩ።