+ -

عَنْ عَائِشَةَ رضي الله عنها قَالَتْ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«الْمَاهِرُ بِالْقُرْآنِ مَعَ السَّفَرَةِ الْكِرَامِ الْبَرَرَةِ، وَالَّذِي يَقْرَأُ الْقُرْآنَ وَيَتَتَعْتَعُ فِيهِ، وَهُوَ عَلَيْهِ شَاقٌّ، لَهُ أَجْرَانِ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 798]
المزيــد ...

ከዓኢሻህ ረዲየሏሁ ዐንሃ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና -እንደተላለፈው፡ "የአሏህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፡
"ቁርአንን አሳምሮ የሚያነብ ሰው የተከበሩና ታዛዥ ከሆኑ መላዕክቶች ጋር ነው፤ ቁርኣንን ሲያነብ ከብዶት እየተቸገረ የሚያነብ ሰው ደሞ ለርሱ ሁለት ምንዳ አለው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 798]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ቁርአንን ሽምደዳውን አሳምሮ፤ አስተማማኝ በሆነ መልኩ፤ ውብና ቆንጆ አድርጎ የሚያነብ ሰው በመጪው ዓለም ያለው ምንዳ ደረጃው ታዛዥና የተከበሩ ከሆኑ መላእክቶች ጋር እንደሆነ፤ ቁርአንን የመሸምደድ አቅሙ ደካማ ስለሆነ ቁርአን ማንበብ በርሱ ላይ ከባድና አስቸጋሪ ሆኖበት እየተንተባተበና እየመላለሰ የሚያነብ ከመሆኑም ጋር ሳያቋርጥ ዘውትር የሚያነብ ሰው ደሞ ለርሱ ሁለት ምንዳ እንዳለው ተናገሩ። አንዱ ምንዳ የማንበቡ ምንዳ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የመላለሰበትና ተቸግሮ የማንበቡ ምንዳ ነው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ምንዳና አጅርን ለማግኘት ቁርአንን በመሸምደድ፤ አሳምሮ በመቅራትና አብዝቶ በማንበብ ላይ መነሳሳቱን፤ ይህንን የፈፀመ ሰውም ደረጃው ከፍ ያለ መሆኑን መገለፁን እንረዳለን።
  2. ቃዲ እንዲህ ብለዋል: "ትርጉሙ ቁርአንን እየመላለሰና እየተንተባተበ ያነበበው አሳምሮ ካነበበው የበዛ ምንዳ አለው ማለት አይደለም። ይልቁኑም አሳምሮ የሚያነበው የበዛና የበለጠ ምንዳ ነው የሚያገኘው። እርሱ ከመልአኮች ጋር ነዋ! ስለሆነም በርካታ ምንዳ ያገኛል። ይህ ደረጃ ደሞ ለማንም አልተወሳም። የአላህን መጽሐፍ ለማንበብ፣ ለመሸምደድ፣ ለማሳመር፣ አብዝቶ ለማንበብና ለማወቅ ትኩረት ያላደረገው አሳምሮ ለማንበብ እስኪበቃ ድረስ ትኩረት እንዳደረገው ሰው እንዴት ሊሆን ይችላል?!"
  3. ኢብኑ ባዝ እንዲህ ብለዋል: "ቁርአንን አሳምሮ በመቅራትና ጥሩ አድርጎ በመሸምደድ በቁርአን ላይ ጎበዝ የሆነ ሰው ታዛዥና የተከበሩ ከሆኑ መልአኮች ጋር ነው። ይህም ማለት በአቀራሩም በተግባሩም ቁርአንን የሚያንፅባርቅ ከሆነ ነው እንጂ በአፉ በማንበቡ ብቻ አይደለም። ይልቁንም አሳምሮ ያነበዋልም በርሱም ይተገብራል። በዚህም እርሱ በቃልም መልዕክቱንም የተገበረ ይሆናል ማለት ነው።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ