عَنْ مُعَاوِيَةَ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«الْمُؤَذِّنُونَ أَطْوَلُ النَّاسِ أَعْنَاقًا يَوْمَ الْقِيَامَةِ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 387]
المزيــد ...

ከሙዓዊያህ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ:
"አዛን አድራጊዎች የትንሳኤ ቀን ከሰዎች ሁሉ አንገተ ረጃጅሞች ናቸው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 387]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ለሶላት የሚጣሩ አዛን አድራጊዎች ስራቸው የላቀ፣ መልካማቸው የበዛና ምንዳቸው የገዘፈ በመሆኑ የትንሳኤ ቀን ከሰዎች ሁሉ አንገተ ረጃጅሞች እንደሚሆኑ ተናገሩ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የአዛን ትሩፋቶችና አዛን በማድረግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. የአዛን ባዮች ልቅናና የትንሳኤ ቀን ደረጃቸው ከፍ ያለ መሆኑ መገለፁን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ቱርክኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الموري Kannadisht الأوكرانية الجورجية المقدونية الخميرية البنجابية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ