عَنْ مُعَاوِيَةَ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«الْمُؤَذِّنُونَ أَطْوَلُ النَّاسِ أَعْنَاقًا يَوْمَ الْقِيَامَةِ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 387]
المزيــد ...

ከሙዓዊያህ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ:
"አዛን አድራጊዎች የትንሳኤ ቀን ከሰዎች ሁሉ አንገተ ረጃጅሞች ናቸው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 387]

ማብራሪያ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ለሶላት የሚጣሩ አዛን አድራጊዎች ስራቸው የላቀ፣ መልካማቸው የበዛና ምንዳቸው የገዘፈ በመሆኑ የትንሳኤ ቀን ከሰዎች ሁሉ አንገተ ረጃጅሞች እንደሚሆኑ ተናገሩ።

ከሐዲሡ የሚቀሰሙ ቁምነገሮች

  1. የአዛን ትሩፋቶችና አዛን በማድረግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. የአዛን ባዮች ልቅናና የትንሳኤ ቀን ደረጃቸው ከፍ ያለ መሆኑ መገለፁን እንረዳለን።
ትርጉሞችን አሳይ
ቋንቋ: الإنجليزية الأوردية الإسبانية ተጨማሪ (35)