عن عبد الله بن عمرو رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«لَيْسَ الْوَاصِلُ بِالْمُكَافِئِ، وَلَكِنِ الْوَاصِلُ الَّذِي إِذَا قُطِعَتْ رَحِمُهُ وَصَلَهَا».
[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...
ከዓብደሏህ ቢን ዓምር ረዲየሏሁ ዓንሁማ እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡
"ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ላደረጉለት መልካም ነገር ምላሹን የሚሰጥ የሆነው አይደለም፤ ይልቁንም ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ዝምድናው በተቆረጠ ጊዜ የሚቀጥል የሆነው ነው።"
Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]
ነቢዩ ﷺ እየነገሩን ያሉት ዝምድናን በመቀጠል የተሟላና ለዘመዶቹም በጎ ሰሪ የሚባለው ላደረጉለት መልካም ነገር መልካሙን በመመለስ የተብቃቃው አይደለም፤ ይልቁንም ዝምድናውን በመቀጠል በኩል የተሟላ የሚባለው ዝምድናው በተቆረጠ ጊዜ የሚቀጥል፤ ሰዎቹ እየከፉበትም ለነርሱ መልካሙን በማድረግ ምላሽ የሚሰጣቸው የሆነ ነው።