عن عبد الله بن عمرو رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«لَيْسَ الْوَاصِلُ بِالْمُكَافِئِ، وَلَكِنِ الْوَاصِلُ الَّذِي إِذَا قُطِعَتْ رَحِمُهُ وَصَلَهَا».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ከዓብደሏህ ቢን ዓምር ረዲየሏሁ ዓንሁማ እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡
"ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ላደረጉለት መልካም ነገር ምላሹን የሚሰጥ የሆነው አይደለም፤ ይልቁንም ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ዝምድናው በተቆረጠ ጊዜ የሚቀጥል የሆነው ነው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ነቢዩ ﷺ እየነገሩን ያሉት ዝምድናን በመቀጠል የተሟላና ለዘመዶቹም በጎ ሰሪ የሚባለው ላደረጉለት መልካም ነገር መልካሙን በመመለስ የተብቃቃው አይደለም፤ ይልቁንም ዝምድናውን በመቀጠል በኩል የተሟላ የሚባለው ዝምድናው በተቆረጠ ጊዜ የሚቀጥል፤ ሰዎቹ እየከፉበትም ለነርሱ መልካሙን በማድረግ ምላሽ የሚሰጣቸው የሆነ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ዝምድናን መቀጠል ሲባል በሸሪዓ የሚፈለግበት ካንተጋ የተቆራረጡትን ስትቀጥል፤ የበደሉህን ይቅር ስትላቸው፤ የነፈጉህን ስትለግሳቸው እንጂ ብድር በመመለስ መልኩ ላደረጉልህ ነገር ተመሳሳዩን ምላሽ መስጠትህ አይደለም።
  2. ዝምድናን መቀጠል የሚፈፀመው በገንዘብ፣ በዱዓእ፣ መልካሙን በማዘዝና ከመጥፎ በመከልከል ረገድ እና መሰል በሆኑ ነገራቶች ለነርሱ በጎ በማድረግ እንዲሁም ክፋትን ከነርሱ በተቻለ መጠን በማስወገድ ነው።
ተጨማሪ