+ -

عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«انْصُرْ أَخَاكَ ظَالِمًا أَوْ مَظْلُومًا». فَقَالَ رَجُلٌ: يَا رَسُولَ اللَّهِ، أَنْصُرُهُ إِذَا كَانَ مَظْلُومًا، أَفَرَأَيْتَ إِذَا كَانَ ظَالِمًا كَيْفَ أَنْصُرُهُ؟ قَالَ: « تَحْجُزُهُ -أَوْ تَمْنَعُهُ- مِنَ الظُّلْمِ؛ فَإِنَّ ذَلِكَ نَصْرُهُ».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 6952]
المزيــد ...

አነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዳስተላለፉት እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ - የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦
"ወንድምህ በዳይም ሆነ ወይም ተበዳይ እርዳው።" አንድ ሰውዬም እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ተበዳይ የሆነ ጊዜ እረዳዋለሁ። እስኪ ንገሩኝ በዳይ በሆነ ጊዜ እንዴት ነው የምረዳው?" እርሳቸውም "ከመበደል ታቅበዋለህ ወይም ትከለክለዋለህ። ይህ እርሱን መርዳት ነው።" ብለው መለሱ።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 6952]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሙስሊም ወንድም በዳይም ሆነ ወይም ተበዳይ እንዲረዳ አዘዙ። አንድ ሰውዬም እንዲህ አለ: የአላህ መልክተኛ ሆይ! ተበዳይ በሆነ ጊዜ በደልን ከርሱ ላይ በማስወገድ እረዳዋለሁ። ንገሩኝ እስኪ በዳይ ከሆነ እንዴት ነው የምረዳው? እርሳቸውም እንዲህ በማለት መለሱ: ከበደል ትከለክለዋለህ፣ እጁን ትይዘዋለህ፣ ትገታዋለህ፣ ታቅበዋለህ። ይህ በሰይጣኑና በመጥፎ በምታዘው ነፍሱ ላይ እያገዝከው ነው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በሙስሊሞች መካከል የእምነታዊ ወንድማማችነት ሀቆች መካከል አንዱን ሀቅ ተገንዝበናል።
  2. የበዳይን እጅ መያዝና ከበደል መከልከል እንደሚገባ እንረዳለን።
  3. ተበዳዮች ሁነውም ይሁን በዳይ ሁነው እርስ በርስ ይረዳዱ የነበሩትን የድንቁርና አስተሳሰብ እስልምና ተፃሮ መምጣቱን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ