عن أبي مَرْثَدٍ الغَنَوِيّ رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«لَا تَجْلِسُوا عَلَى الْقُبُورِ، وَلَا تُصَلُّوا إِلَيْهَا».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቡ መርሠድ አልጘነዊይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
'መቃብሮች ላይ አትቀመጡ! ወደርሷም አትስገዱ!'"

ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መቃብሮች ላይ ከመቀመጥ ከለከሉ።
ይህም ወደ መቃብሮች ከመስገድ እንደከለከሉት ነው። ቀብሩ ወደ ሰጋጁ ቂብላ አቅጣጫ መሆኑን ይመስል ማለት ነው። ይህም የተከለከለው ወደ ሺርክ ከሚያዳርሱ ምክንያቶች አንዱ ስለሆነ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በሐዲስ እንደተረጋገጠው የጀናዛ ሶላት ካልሆነ በቀር በመቃብር ስፍራ ወይም በመቃብሮች መካከል ወይም ወደ መቃብር ዙሮ መስገድ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. ወደ መቃብር መስገድ የተከለከለው የሺርክን መዳረሻዎች ለመዝጋት ነው።
  3. ኢስላም በመቃብር ወሰን ማለፍንም መቃብር ማዋረድንም ከልክሏል። ወሰን ማለፍም ማሳነስም የለምና።
  4. ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "የሙትን አጥንት መስበር በህይወት እንደመስበር ነው።" ስላሉ የሙስሊም ክብር ከሞተ በኋላም ዘላቂ ነው።