عَنْ ‌عَائِشَةَ رَضِيَ اللهُ عَنْهَا قَالَتْ:
تَلَا رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ هَذِهِ الْآيَةَ: {هُوَ الَّذِي أَنْزَلَ عَلَيْكَ الْكِتَابَ مِنْهُ آيَاتٌ مُحْكَمَاتٌ هُنَّ أُمُّ الْكِتَابِ وَأُخَرُ مُتَشَابِهَاتٌ فَأَمَّا الَّذِينَ فِي قُلُوبِهِمْ زَيْغٌ فَيَتَّبِعُونَ مَا تَشَابَهَ مِنْهُ ابْتِغَاءَ الْفِتْنَةِ وَابْتِغَاءَ تَأْوِيلِهِ، وَمَا يَعْلَمُ تَأْوِيلَهُ إِلَّا اللَّهُ، وَالرَّاسِخُونَ فِي الْعِلْمِ يَقُولُونَ آمَنَّا بِهِ كُلٌّ مِنْ عِنْدِ رَبِّنَا وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّا أُولُو الْأَلْبَابِ} [آل عمران: 7]. قَالَتْ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «فَإِذَا رَأَيْتِ الَّذِينَ يَتَّبِعُونَ مَا تَشَابَهَ مِنْهُ فَأُولَئِكَ الَّذِينَ سَمَّى اللهُ، فَاحْذَرُوهُمْ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

የምእመናን እናት ዓኢሻ -አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና- እንዲህ ብላለች፦
የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ይህቺን አንቀፅ አነበቡ {እርሱ ያ በአንተ ላይ መጽሀፉን ያወረደ ነው። ከእርሱ (ከመፅሀፉ) ግልጽ የሆኑ አንቀጾች አሉ። እነሱ የመጽሐፉ መሠረቶች ናቸው። ሌሎችም ተመሳሳዮች አሉ። እነዚያማ በልቦቻቸው ውስጥ ጥመት ያለባቸው ሰዎች ማሳሳትን ለመፈለግና ማጣመምን ለመፈለግ ከርሱ የተመሳሰለውን ይከታተላሉ። (ትክክለኛ) ፍቺውንም አላህ ብቻ እንጂ ሌላ አያውቀውም። በዕውቀትም የጠለቁት "በርሱ አምነናል፤ ሁሉም ከጌታችን ዘንድ ነው" ይላሉ። የአእምሮ ባለቤቶችም እንጅ (ሌላው) አይገሰጽም።} [ኣሉ ዒምራን: 7] ቀጥለው የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ አሉ፦ " እነዚያ ከቁርአን የተመሳሰለውን የሚከተሉትን ከተመለከትሽ አላህ ተጠንቀቁዋቸው ብሎ የጠቀሳቸው እነሱ ናቸው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ይህቺን አንቀፅ አነበቡ {እርሱ ያ በአንተ ላይ መጽሀፉን ያወረደ ነው። ከእርሱ (ከመጽሐፉ) ግልጽ የሆኑ አንቀጾች አሉ። እነሱ የመጽሀፉ መሠረቶች ናቸው። ሌሎችም ተመሳሳዮች አሉ። እነዚያማ በልቦቻቸው ውስጥ ጥመት ያለባቸው ሰዎች ማሳሳትን ለመፈለግና ማጣመምን ለመፈለግ ከርሱ የተመሳሰለውን ይከታተላሉ። (ትክክለኛ) ፍቺውንም አላህ ብቻ እንጂ ሌላ አያውቀውም። በዕውቀትም የጠለቁት "በርሱ አምነናል፤ ሁሉም ከጌታችን ዘንድ ነው" ይላሉ። የአእምሮ ባለቤቶችም እንጅ (ሌላው) አይገሰጽም።} አላህ በዚህ አንቀፅ ውስጥ በነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ላይ ቁርአንን ያወረደው እርሱ አላህ መሆኑን ይናገራል። ከቁርአን ውስጥም መልእክታቸው ግልፅ የሆኑና ያለምንም ማደናገር ድንጋጌያቸው የታወቁ አንቀፆች አሉ። እርሱም የመጽሐፉ መሰረትና በልዩነት ወቅት የሚዳኝ ምንጭ ነው። ቁርኣን ውስጥ በርካታ ትርጓሜን የሚሰጡ አሻሚ አንቀፆችም አሉ። እነዚህ አንቀፆችን አንዳንድ ሰዎች ወይ በትርጓሜዋ ይደናገራሉ ወይም ከሌላ አንቀፅ ጋር እንደተጋጨች ያስባሉ። ቀጥሎ አላህ ሰዎች ከነዚህ አንቀፆች ጋር ያላቸውን መስተጋብር አብራራ። እነዚያ ልቦቻቸውን ከሀቅ መጣመም የተጠናወተው ሰዎች ሰውን ማሳሳትና ብዥታን ማቀጣጠል በመፈለግ ግልፅ የሆኑትን አንቀፆች በመተው አሻሚ የሆኑትን አንቀፆች ይወስዳሉ። ይህንንም ያደረጉት ዝንባሌያቸውን በሚስማማ መልኩ መፍታትን በመፈለጋቸው ነው። በእውቀት የፀኑት ግን እነዚህን አሻሚ አንቀፆች ያውቃሉ ፍቻቸውንም ወደ ግልፅ የሆኑ አንቀፆች ይመልሳሉ፤ ከአላህ ዘንድ ስለሆነም እርስ በርስ ምንም መጋጨትና ማደናገር ሊከሰት እንደማይችል ያምናሉ። ነገር ግን የንፁህ አይምሮ ባለቤት ካልሆነ በቀር ሊገሰፅም ሆነ ሊመከር እንደማይችል አላህ ገለፀ። ቀጥለው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ለአማኞች እናት ዓኢሻህ - አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና - "እነዚያ አሻሚ አንቀፆችን የሚከታተሉትን ከተመለከተች አላህ {እነዚያማ በልቦቻቸው ውስጥ ጥመት ያለባቸው} በማለት የጠቀሳቸው ናቸውና ተጠንቀቋቸው አታድምጧቸው።" አሏት።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከቁርአን አንቀፆች ግልፅ የሚባሉት መልእክቱ ፍንትው ያለና ትርጉሙ ግልፅ የሆነ ነው። አሻሚ የሚባሉት ደግሞ ከአንድ በላይ በርካታ ትርጓሜ ያዘለ እንዲሁም ለመረዳት ጥናትና ግንዛቤ ያስፈለገው አንቀፅ ነው።
  2. የጥመትና የቢድዐ ባለቤቶችን፣ ሰዎችን ለማሳሳትና ጥርጣሬ ውስጥ ለመክተት አወናባጅ ነጥቦችን የሚጥል ሰውን ከመቀላቀል መጠንቀቅ፤
  3. የአንቀፁ መጨረሻ ክፍል ላይ {የአእምሮ ባለቤቶችም እንጅ (ሌላው) አይገሰጽም።} በሚለው የአላህ ንግግር ውስጥ ጠማሞችን መቃወምና በእውቀት የጠለቁትን ማሞገስ አለ። ማለትም፦ ያልተገሰፀና ያልተመከረ ስሜቱንም የተከተለ ከአእምሮ ባለቤቶች አይደለም ማለቱ ነው።
  4. አሻሚ አንቀጾችን መከታተል ለልቦና ጥመት መንስኤ ነው።
  5. ትርጉማቸው የማይገባ የሆኑ አሻሚ አንቀጾችን ወደ ግልፅ አንቀጾች መመለስ ግዴታ መሆኑን፤
  6. አላህ ሰዎችን ለመፈተንና የኢማን ባለቤቶች ከጥመት ባለቤቶች እንዲለዩ የቁርአንን ከፊል ግልፅ ከፊሉን ደግሞ አሻሚ አድርጓል።
  7. ቁርአን ውስጥ አሻሚ አንቀጾች መካተታቸው ዑለሞች ከሌላው አንፃር ያላቸውን ደረጃ የሚገልፅና አይምሮ አቅሟ የተገደበ መሆኑን አውቃ ለፈጣሪዋ እጅ መስጠትና ድክመቷን ማወቅ እንዳለባት እንረዳለን።
  8. በዕውቀት መጥለቅ ያለው ደረጃና በዕውቀት መፅናት አስፈላጊነቱን እንረዳለን።
  9. {(ትክክለኛ) ፍቺውንም አላህ ብቻ እንጂ ሌላ አያውቀውም። በዕውቀትም የጠለቁትም} በሚለው አንቀፅ ላይ "አላህ" የሚለው ላይ ሲደርስ በመቆም ዙሪያ የተፍሲር ልሂቃን ዘንድ ሁለት አቋም አለ። "አላህ" የሚለው ጋር ሲደርስ የቆመ ፍቺውን በማለት የሚፈለገው:- ለማወቅ የማይቻል የሆኑ የአንድን ነገር ትክክለኛ ምንነትን ፍቺ አላህ ብቻ እንጂ አያውቀውም። ለምሳሌ ስለነፍስ፣ ስለቂያማ ዕለትና ሌሎችም አላህ በዕውቀቱ የተነጠለበት ጉዳዮች። በእውቀት የጠለቁት ግን በሱ ያምናሉም ይቀበላሉም በዚህም ምክንያት ይድናሉ።
  10. "አላህ" የሚለው ጋር ሲደርስ ያልቆመ "ፍቺውን" በማለት የተፈለገው "ትርጓሜውን" ማለት ይሆናል። ትርጓሜውን አላህና በእውቀት የጠለቁት ያውቁታል። ያምኑበታልም ወደ ግልፅ የቁርአን አንቀፅም ይመልሱታል ማለት ይሆናል።