عَنْ ‌عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«الْيَهُودُ مَغْضُوبٌ عَلَيْهِمْ، وَالنَّصَارَى ضُلَّالٌ».

[صحيح] - [رواه الترمذي]
المزيــد ...

ከዓዲይ ቢን ሓቲም እንደተላለፈው: "ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ፦
"አይሁዶች ቁጣ የሰፈነባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳሳቱ ናቸው።"

Sahih/Authentic. - [At-Tirmidhi]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አይሁዶች እውነትን እያወቁ ባለመተግበራቸው አላህ የተቆጣባቸው ህዝቦች እንደሆኑ ተናገሩ። ክርስቲያኖች ደግሞ ያለ ዕውቀት የሚሰሩ ስለሆኑ የተሳሳቱ ህዝቦች ናቸው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ዕውቀትና ተግባርን ሰብስቦ መሄድ ቁጣ ከሰፈነባቸውም ከተሳሳቱትም ሰዎች መንገድ መዳኛ መሆኑን እንረዳለን።
  2. ከአይሁዶችና ክርስቲያኖች መንገድ መጠንቀቅና ቀጥተኛ የሆነውን የኢስላምን ጎዳና አጥብቀን መያዝ እንዳለብን እንረዳለን።
  3. በመሰረቱ አይሁዶችም ክርስቲያኖችም የተሳሳቱና ቁጣ የሰፈነባቸው ህዝቦች ናቸው። ነገር ግን ልዩ መገለጫቸው የአይሁዶቹ ቁጣ የሰፈነባቸው መሆናቸው ሲሆን የክርስቲያኖች ልዩ መገለጫ ደግሞ መሳሳታቸው ነው።
ተጨማሪ