عن أبي هريرة رضي الله عنه قال:
سُئِلَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَنْ أَكْثَرِ مَا يُدْخِلُ النَّاسَ الْجَنَّةَ، فَقَالَ: «تَقْوَى اللهِ وَحُسْنُ الْخُلُقِ»، وَسُئِلَ عَنْ أَكْثَرِ مَا يُدْخِلُ النَّاسَ النَّارَ فَقَالَ: «الْفَمُ وَالْفَرْجُ».

[حسن صحيح] - [رواه الترمذي وابن ماجه وأحمد]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በአብዛኛው ሰዎችን ጀነት ስለሚያስገባው ነገር ተጠየቁ፤ እሳቸውም "አላህን መፍራት እና መልካም ስነምግባር ነው።" አሉ። በአብዛኛው ሰዎችን እሳት ስለሚያስገባቸው ነገርም ተጠየቁ። እሳቸውም "ምላስና ብልት ነው።" አሉ።

Hasan Sahih /Sound-Authentic. - [At-Tirmidhi]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጀነት የሚያስገቡ ትልልቅ ምክንያቶች ሁለት መሆናቸውን ገለፁ። እነሱም:
አላህን መፍራትና መልካም ስነምግባር ናቸው።
አላህን መፍራት: በአንተና በአላህ ቅጣት መካከል መጠበቂያ ማድረግህ ነው። ይህም ትእዛዙን በመፈፀምና ክልከላውን በመራቅ ነው።
መልካም ስነምግባር ደሞ: ፊትን ፈታ በማድረግ ፣ መልካምን በመለገስና ከማወክ በመቆጠብ ነው።
እሳት የሚያስገቡት ትልልቅ ምክንያቶች ደግሞ ሁለት ናቸው። እነሱም:
ምላስና ብልት ናቸው።
ከምላስ ወንጀሎች መካከል:- ውሸት፣ ሀሜት፣ ወሬ ማዋሰድና ሌሎችም ናቸው።
ከብልት ወንጀሎች መካከል ደሞ:- ዝሙት፣ ግብረሰዶምና ሌሎችም ይጠቀሳሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ጀነት መግባት ከአላህ ትእዛዝ ጋር የተገናኙ ምክንያቶች አሉት። ከነሱም መካከል:- አላህን መፍራትን ይመስል። ከሰዎች ጋር የተገናኙ ምክንያቶችም አሉት። ከነሱም መካከል:- መልካም ስነምግባርን ይመስል።
  2. ምላስ እሳት ከመግቢያ ምክንያቶች መካከል ስለሆነ በባለቤቱ ላይ አደገኛ መሆኑ፤
  3. የስሜት ተገዢ መሆንና ፀያፍ ወንጀሎችን መስራት በአብዛኛው እሳት የመግቢያ ምክንያቶች መካከል አንዱ ስለሆነ በሰው ላይ አደጋ መሆኑን እንረዳለን።