عن أبي موسى الأشعري رضي الله عنه عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«مَنْ حَمَلَ عَلَيْنَا السِّلَاحَ فَلَيْسَ مِنَّا».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሙሳ አልአሽዐሪይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"መሳሪያውን በኛ ላይ ያነሳ ከኛ አይደለም።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለማስፈራራት ወይም ንብረታቸውን ለመቀማት በሙስሊሞች ላይ መሳሪያ ከማንሳት አስጠነቀቁ። ያለ አግባብ ይህንን የፈፀመም ትልቅ ሀጢአትንና ወንጀልን መፈፀሙን ለዚህ ከባድ ዛቻም መጋረጡን አሳሰቡ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሙስሊም ከሙስሊም ወንድሙ ጋር መጋደሉ ብርቱ ማስጠንቀቂያ የመጣበት ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን።
  2. በምድር ላይ ከሚሰሩ ትላልቅ ወንጀሎችና ብክለቶች መካከል መሳሪያን በሙስሊሞች ላይ ማንሳትና በመግደል ማበላሸት ነው።
  3. የተጠቀሰው ዛቻ ወሰን አላፊዎችን፣ አጥፊዎችንና ሌሎችም የመሳሰሉትን በሀቅ (በሸሪዓ በተፈቀደ ምክንያት) መጋደልን አያካትትም።
  4. ለቀልድ እንኳ ቢሆን ሙስሊሞችን በመሳሪያ ወይም በሌላ ነገር ማስፈራራት መከልከሉን እንረዳለን።