عن أبي مسعود رضي الله عنه عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«إِذَا أَنْفَقَ الرَّجُلُ عَلَى أَهْلِهِ يَحْتَسِبُهَا فَهُوَ لَهُ صَدَقَةٌ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ መስዑድ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድለትና- እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
"ሰውዬው (ምንዳ እንደሚያገኝበት) እያሰበ ለቤተሰቡ ወጪ ያወጣ ጊዜ ለርሱ ምፅዋት ትሆንለታለች።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ሰውዬው እንደሚስቱ፣ ወላጆቹ፣ ልጁና ሌሎችንም እነርሱ ላይ ወጪ ማውጣት ግዴታ ለሆነበት አካል ሲሰጥ ወደ አላህ መቃረብንና አላህ ዘንድ ምንዳን እያሰበ ከሆነ ለርሱ የምፅዋት ምንዳ እንደሚሰጠው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ለቤተሰቦች ወጪ በማውጣት ምንዳና አጅር እንደሚገኝ እንረዳለን።
  2. ሙእሚን የሆነ ሰው በስራው የአላህን ፊትና እርሱ ዘንድ ያለውን ምንዳና አጅር እንደሚፈልግ እንረዳለን።
  3. በሁሉም ስራዎች መልካምን ኒያ ማድረግ ይገባል። ከነዚህም ስራዎች መካከል ለቤተሰቦች ወጪ በምናወጣ ጊዜ አንዱ ነው።