+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«إِنَّ اللهَ إِذَا أَحَبَّ عَبْدًا دَعَا جِبْرِيلَ فَقَالَ: إِنِّي أُحِبُّ فُلَانًا فَأَحِبَّهُ، قَالَ: فَيُحِبُّهُ جِبْرِيلُ، ثُمَّ يُنَادِي فِي السَّمَاءِ فَيَقُولُ: إِنَّ اللهَ يُحِبُّ فُلَانًا فَأَحِبُّوهُ، فَيُحِبُّهُ أَهْلُ السَّمَاءِ، قَالَ ثُمَّ يُوضَعُ لَهُ الْقَبُولُ فِي الْأَرْضِ، وَإِذَا أَبْغَضَ عَبْدًا دَعَا جِبْرِيلَ فَيَقُولُ: إِنِّي أُبْغِضُ فُلَانًا فَأَبْغِضْهُ، قَالَ فَيُبْغِضُهُ جِبْرِيلُ، ثُمَّ يُنَادِي فِي أَهْلِ السَّمَاءِ إِنَّ اللهَ يُبْغِضُ فُلَانًا فَأَبْغِضُوهُ، قَالَ: فَيُبْغِضُونَهُ، ثُمَّ تُوضَعُ لَهُ الْبَغْضَاءُ فِي الْأَرْضِ».

[صحيح] - [صحيح مسلم] - [صحيح مسلم: 2637]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
«አላህ አንድን ባሪያ የወደደው ጊዜ ጂብሪልን ይጠራውና እንዲህ ይለዋል: "እኔ እከሌን እወደዋለሁና ውደደው።" ጂብሪልም ይወደዋል። ቀጥሎ ጂብሪል ሰማይ ውስጥ እንዲህ በማለት ይጣራል: "አላህ እከሌን ይወደዋልና ውደዱት።" የሰማይ ነዋሪዎችም ይወዱታል። ከዚያም ምድር ላይ ተቀባይነት ይኖረዋል። አላህ አንድን ባሪያ የጠላ ጊዜም ጂብሪልን በመጥራት እንዲህ ይለዋል: "እኔ እከሌን እጠላዋለሁና ጥላው።" ጂብሪልም ይጠላዋል። ቀጥሎም ጂብሪል ለሰማይ ነዋሪዎች እንዲህ በማለት ይጣራል: "አላህ እከሌን ይጠላዋልና ጥሉት።" እነርሱም ይጠሉታል። ከዚያም ምድር ላይ ተጠይነትን ይኖርበታል።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2637]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አላህ አንድን ትእዛዙን ታዛዥና ክልከላውን የሚርቅ አማኝ ባሪያውን የወደደ ጊዜ ጂብሪልን ይጣራል። አላህ እከሌን ይወደዋልና ውደደው። የመልአክቶች አለቃው ጂብሪል ዓለይሂ ሰላም ይወደዋል። ጂብሪልም ለሰማይ መልአክቶች ይጣራል። ጌታችሁ እከሌን ይወደዋልና ውደዱት። የሰማይ ነዋሪዎችም ይወዱታል። ቀጥሎ በአማኞች ቀልብ ውስጥ ለርሱ ውዴታን፣ ወደርሱ የመሳብንና በርሱ የመደሰትን ተቀባይነት እንዲኖረው ይደረጋል። አላህ አንድን ባሪያ የጠላ ጊዜም ጂብሪልን ይጣራል። እኔ እከሌን ጠልቼዋለሁና ጥላው። ጂብሪልም ይጠላዋል። ቀጥሎ ጂብሪል የሰማይን ነዋሪዎች ይጣራል። ጌታችሁ እከሌን ይጠላዋልና ጥሉት። እነርሱም ይጠሉታል። ከዚያም በአማኞች ቀልብ ውስጥ ለርሱ ጥላቻ እንዲኖር ይደረጋል።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አቡ ሙሐመድ ቢን አቢ ጀምራ እንዲህ ብለዋል: "ከመልአክቶች ሁሉ ከሌላው አስቀድሞ ጉዳዩን በጂብሪል መጀመሩ ከመልአክቶች ሁሉ እርሱ አላህ ዘንድ ያለውን ከፍ ያለ ደረጃ ለመግለፅ ነው።"
  2. አላህ የወደደውን ሰው የሰማይና የምድር ነዋሪዎችም ይወዱታል። አላህ የጠላው ሰውም የሰማይና የምድር ነዋሪዎችም ይጠሉታል።
  3. ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: (ምድር ላይ ተቀባይነት ይኖረዋል) የሚለው የግድ ሁሉም ዘንድ ተወዳጅነትን አይጠቁምም። ይልቁንም አላህ በምድር ላይ እንዲኖረው የሻለትን ያህል ቅቡልነት ነው የሚኖረው። ክፉዎችች ለመልካሞች ያላቸው ጠላትነት እየታወቀ እንዴት አጠቃላይ ውዴታ ይኖረዋል?!
  4. የተለያዩ አይነቶችን መልካም ስራዎች ግዴታም ይሁን ሱና አሟልቶ በመስራት ላይ መነሳሳቱንና ወንጀሎችና ቢድዓዎች የአላህን ቁጣ የሚያመጡ ስለሆኑ መጠንቀቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
  5. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ከዚህ ሐዲሥ ከምንወስዳቸው አስተምህሮቶች መካከል በሰዎች ቀልብ መወደድ በአላህ የመወደድ ምልክት ነው። ይህንንም የጀናዛ ምዕራፍ ውስጥ "እናንተ በምድር የአላህ ምስክር ናችሁ።" በሚል የተዘገበው ሐዲሥ ያጠናክረዋል።"
  6. ኢብኑል ዐረቢ አልማሊኪይ እንዲህ ብለዋል: "የምድር ነዋሪዎች ሲባል የሚፈለገው ሰውዬውን የሚያውቁት ማለት ነው እንጂ የማያውቁትና ስለርሱ ሰምተው የማያውቁትም ይወዱታል ማለት አይደለም።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ተጨማሪ