عن عرفجة رضي الله عنه قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول:
«مَنْ أَتَاكُمْ وَأَمْرُكُمْ جَمِيعٌ عَلَى رَجُلٍ وَاحِدٍ، يُرِيدُ أَنْ يَشُقَّ عَصَاكُمْ، أَوْ يُفَرِّقَ جَمَاعَتَكُمْ، فَاقْتُلُوهُ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከዐርፈጀህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻዋለሁ:
"ጉዳያችሁ በአንድ መሪ የተሰበሰበ ሁኖ ሳለ አንድነታችሁን ሊሰነጥቅ ወይም ህብረታችሁን ሊበታትን የመጣ ሰውን ግደሉት።"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ሙስሊሞች በአንድ መሪና በአንድ ህብረት የተሰበሰቡ ሆነው ሳለ ከዚያም መሪነቱን መገዳደር ፈልጎ ወይም ሙስሊሞችን ከአንድ ህብረት በላይ እንዲሆኑ መበታተን ፈልጎ የመጣን ሰው አደጋውን ለመከላከልና የሙስሊሞችን ደም ለመጠበቅ ሲባል በነርሱ ላይ መከልከልና መጋደል ግዴታ እንደሆነ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከወንጀል ውጪ በሆኑ ጉዳዮች የሙስሊሞችን መሪ መስማትና መታዘዝ ግዴታ መሆኑን እና በርሱ ላይ አምፆ መውጣትም ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. የሙስሊሞች መሪ ላይና ህብረታቸው ላይ አምፆ የወጣ ሰውን ክብሩና ዘሩ ምንም ያህል የላቀ ቢሆን እንኳ እሱን መዋጋት ግዴታ ነው።
  3. በአንድነትና አለመለያየት፣ አለመበታተን ላይ መነሳሳቱን (መበረታታቱን) እንረዳለን።