عن النعمان بن بَشِير رضي الله عنه قال: سمعت النبيَّ صلى الله عليه وسلم يقول:
«الدُّعَاءُ هُوَ الْعِبَادَةُ»، ثُمَّ قَرَأَ: «{وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ} [غافر: 60]».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي وابن ماجه وأحمد]
المزيــد ...

ከኑዕማን ቢን በሺር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "ነቢዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ:
'ዱዓእ እሱ አምልኮ ነው።' ከዚያም {ጌታችሁም አለ "ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና። እነዚያ እኔን ከመግገዛት የሚኮሩት ተዋራጆች ሆነው ገሀነምን በእርግጥ ይገባሉ።"} [ጋፊር: 60] የሚለውን አነበቡ።"

Sahih/Authentic. - [Ibn Maajah]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዱዓእ አምልኮ እንደሆነ ተናገሩ። በዱንያና በአኺራዊ ጉዳዮች የሚጠቅመውን ነገር እንዲሰጠውና የሚጎዳውን ነገር እንዲከላከልለት አላህ የሚጠየቅበት ልመናዊ ዱዓም ይሁን፤ ማንኛውም ውጫዊና ውስጣዊ ንግግርም ተግባርም አላህ የሚወዳቸውና የሚያስደስተው ልባዊ፣ አካላዊና ገንዘባዊ አምልኮዎችን የሚያደርጉበት አምልኳዊ ዱዓእም ያው ነው። እነዚህ የዱዓእ አይነቶችም ለአላህ ብቻ ጥርት ተደርገው መፈፀማቸው ግዴታ ነው።
ከዚያም ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ለዚህ ንግግራቸው የአላህን ንግግር ማስረጃ አደረጉ። አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ጌታችሁም አለ "ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና። እነዚያ እኔን ከመግገዛት የሚኮሩት ተዋራጆች ሆነው ገሀነምን በእርግጥ ይገባሉ።"}

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ዱዓእ የአምልኮ መሰረት በመሆኑ ከአላህ ውጪ ለሆነ መስጠት አይፈቀድም።
  2. ዱዓእ እውነተኛ ባርነትን፣ የጌታን መብቃቃትና ችሎታ እውቅና መስጠትን እና የባሪያን ወደ አላህ ፈላጊነቱን ያካተተ ነው።
  3. ከአላህ አምልኮ በመኩራትና ዱዓእን በመተው ምንዳ ዙሪያ ብርቱ ዛቻ መምጣቱን እንረዳለን። አላህን ከመለመን የሚኮሩ ሰዎች ጀሀነም የተናነሱና የተዋረዱ ሆነው ይገባሉ።