+ -

عَنْ عِيَاضِ بْنِ حِمَارٍ أَخِي بَنِي مُجَاشِعٍ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ: قَامَ فِينَا رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ ذَاتَ يَوْمٍ خَطِيبًا، فَقَالَ: وَسَاقَ الْحَدِيثَ وَفِيهِ:
«وَإِنَّ اللهَ أَوْحَى إِلَيَّ أَنْ تَوَاضَعُوا حَتَّى لَا يَفْخَرَ أَحَدٌ عَلَى أَحَدٍ، وَلَا يَبْغِي أَحَدٌ عَلَى أَحَدٍ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2865]
المزيــد ...

የበኒ ሙጃሺዕ ወንድም ከሆነው ከዒያድ ቢን ሒማር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «አንድ ቀን የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ኹጥባ ለማድረግ ተነሱ። ከተናገሯቸው ንግግሮች መካከልም:
"አንዱ በአንዱ ላይ በማይፎክርና አንዱ በአንዱ ላይ ወሰን በማይተላለፍበት ልክ እንድትተናነሱ አላህ ወደኔ ራዕይ አውርዷል።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2865]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ለባልደረቦቻቸው ኹጥባ ለማድረግ ተነሱ። ከተናገሯቸው መካከልም: አላህ እንዲህ ብሎ ራዕይ ማውረዱን ተናገሩ: ሰዎች በዘራቸው ወይም በገንዘባቸው ወይም ከዛ ውጪ ባሉ ነገሮች አንዱ በአንዱ ላይ ልቅናን፣ ኩራትንና ክብርን ለራሱ በማድረግ ሳይፎክርና አንዱ በአንዱ ላይ ወሰን ሳይተላለፍ ለፍጥረታት ራሳቸውን ዝቅ በማድረግና ማንነታቸውን በማለዘብ እርስ በርሳቸው መተናነሳቸው ግዴታ ነው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከሐዲሡ ከምንወስዳቸው ቁምነገሮች መካከል በመተናነስ ላይ፣ ባለመኩራትና በሰዎች ላይ አለመንጠራራትን ያነሳሳል።
  2. ወሰን ማለፍና መመፃደቅ መከልከሉን እንረዳለን።
  3. ለአላህ መተናነስ ሁለት ትርጓሜዎች አሉት: የመጀመሪያው ትርጓሜ: ለአላህ ዲን መተናነስ ነው። ከእስልምና በላይ ራስን ከፍ አለማድረግ፣ እስልምናንና ህግጋቶቹን ከመፈፀም አለመኩራት ነው። ሁለተኛው: ለአላህ ብሎ ለአላህ ባሮች መተናነስ ነው። እነርሱን በመፍራትና እነርሱ ዘንድ ያለውን በመከጀል ሳይሆን ለአላህ ብቻ ብሎ ለነርሱ መተናነስ ነው።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ