عَنْ سَلَمَةَ بْنِ الْأَكْوَعِ رضي الله عنه:
أَنَّ رَجُلًا أَكَلَ عِنْدَ رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ بِشِمَالِهِ، فَقَالَ: «كُلْ بِيَمِينِكَ»، قَالَ: لَا أَسْتَطِيعُ، قَالَ: «لَا اسْتَطَعْتَ»، مَا مَنَعَهُ إِلَّا الْكِبْرُ، قَالَ: فَمَا رَفَعَهَا إِلَى فِيهِ.

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከሰለማ ቢን አክወዕ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው፦
"አንድ ሰውዬ የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ በግራ እጁ በላ። እርሳቸውም 'በቀኝህ ብላ።' አሉት። እርሱም 'አልችልም!' አላቸው። እርሳቸውም 'አያስችልህ!' አሉት። ኩራት እንጂ ሌላ አልከለከለውም። ሰለማ እንዲህ አለ '(ከዛ በኃላ) እጁን ወደ አፉ ማንሳት አልቻለም።' "

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አንድ ሰው በግራ እጁ ሲበላ ተመለከቱትና በቀኝ እጁ እንዲበላ አዘዙት። ሰውዬውም በኩራትና በውሸት በቀኝ እጁ መብላት እንደማይችል መለሰላቸው። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በቀኝ እጁ መመገብ አሏህ እንዳያስችለው በርሱ ላይ ዱዓ አደረጉበት። ቀኝ እጁን ሽባ በማድረግ አላህ የነቢዩን ዱዓ ተቀበለ። ከዚህ በኋላም ምግብ ወይም መጠጥ ወደ አፉ ማንሳት አልቻለም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በቀኝ እጅ መብላት ግዴታ መሆኑንና በግራ መብላት ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. የሸሪዓን ህግጋት ተግባራዊ ከማድረግ መኩራራት ባለቤቱን ለቅጣት የተገባ ያደርገዋል።
  3. አላህ ለነቢዩ ሙሐመድ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዱዓቸውን በመቀበል ማክበሩን እንረዳለን።
  4. በመልካም ማዘዝና ከመጥፎ መከልከል በሁሉም ሁኔታ ላይ በመመገብ ወቅት እንኳ ሳይቀር መደንገጉን እንረዳለን።