عن عائشة وعبد الله بن عباس رضي الله عنهما قالا:
لَمَّا نَزَلَ بِرَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ طَفِقَ يَطْرَحُ خَمِيصَةً لَهُ عَلَى وَجْهِهِ، فَإِذَا اغْتَمَّ بِهَا كَشَفَهَا عَنْ وَجْهِهِ، فَقَالَ وَهُوَ كَذَلِكَ: «لَعْنَةُ اللَّهِ عَلَى اليَهُودِ وَالنَّصَارَى، اتَّخَذُوا قُبُورَ أَنْبِيَائِهِمْ مَسَاجِدَ» يُحَذِّرُ مَا صَنَعُوا.

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከእናትችን ዓኢሻና ዐብደላህ ቢን ዓባስ - (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦
"የሞት መልዐክ በአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ላይ የወረደ ጊዜ ፊታቸው ላይ ጨርቃቸውን ጣል ማድረግ ጀመሩ ፤ ሲያፍናቸው ደግሞ ይገልጧት ነበር ፤ በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ 'በአይሁድ እና ክርስቲያኖች ላይ የአላህ እርግማን ይውረድ ! የነቢያቶቻቸውን መቃብር መስገጃ አድርገው ያዙ።' አሉ፤ ከሰሩት ስራ እያስጠነቀቁ። '"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

እናታችን ዓኢሻና ኢብኑ ዓባስ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሞት የቀረባቸው ጊዜ የጨርቅ ቁራጭ ፊታቸው ላይ ጣል ያደርጉ እንደነበርና በሞት ስካር ሳቢያ ለመተንፈስ ያስቸገራቸው ጊዜም ከፊታቸው ያስወግዱት እንደነበር ነገረችን። በዚህ ከባድ ሁኔታ ላይ እያሉ አላህ አይሁድና ክርስቲያኖችን እንደረገመ፤ ከእዝነቱም እንዳራቀ፤ ይህም በነቢያቶቻቸው መቃብር ላይ መስገጃ በመገንባታቸው ምክንያት መሆኑን ነገረችን። የጉዳዩ አደገኛነት ከባድ ባልነበር በእንደዚ አይነት ሁኔታ ላይ ሆነው አይጠቅሱትም ነበር። ስለዚህም ይህ የአይሁዶችና ክርስቲያኖች ድርጊት እንዲሁም በአላህ ላይ ወደ ማጋራት የሚያዳርስ ነውና ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በዚህ መሰል ድርጊቶች ላይ ከነርሱ ጋር መመሳሰልን ከለከሉ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የነቢያቶችንና ደጋጎችን መቃብር ለአላህ የሚሰገድበት መስገጃ አድርጎ መያዝ ወደ ሺርክ የሚያዳርስ ስለሆነ መከልከሉን እንረዳለን።
  2. የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በተውሒድ ላይ ያላቸው ትኩረትና ጥንቃቄ የበረታ መሆኑንና መቃብርን ማላቅም ወደ ሺርክ ስለሚያዳርስ መስጋታቸውን እንረዳለን።
  3. አይሁዶችንና ክርስቲያኖችን መርገም እንዲሁም ቀብር ላይ በመገንባትና መቃብርን መስገጃ አድርጎ በመያዝ የነርሱን ድርጊት አምሳያ የሰራን ሰውም መርገም እንደሚፈቀድ እንረዳለን።
  4. በመቃብር ላይ መገንባት የአይሁዶችና ክርስቲያኖች ሱና መሆኑንና ሐዲሡ ከነርሱ ጋር መመሳሰልንም ይከለክላል።
  5. መስገጃ ባይገነባበት እንኳ እርሱ ዘንድ መስገድና ወደርሱ ዙሮ መስገድ መቃብርን መስገጃ አድርጎ መያዝ ውስጥ ይካተታል።