عن عُقبة بن عامر الجُهني رضي الله عنه قال: قال رسولُ الله صلَّى الله عليه وسلم:
«الجاهِرُ بالقرآن كالجاهِرِ بالصَّدَقَةِ، والمُسِرُّ بالقرآن كالمُسِرِّ بالصَّدَقَة».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي]
المزيــد ...

ዑቅባ ቢን ዓሚር አልጁሀኒይ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦
"ቁርኣንን ድምፁን ከፍ አድርጎ የሚያነብ ምፅዋትን በይፋ እንደሚመፀውት አምሳያ ነው፤ ቁርኣንን በዝግታ የሚያነብ ምፅዋትን በድብቅ እንደሚመፀውት አምሳያ ነው።"

Sahih/Authentic. - [Abu Dawood]

ትንታኔ

ቁርኣንን በይፋ የሚያነብ ምፅዋት በይፋ እንደሚሰጥ አምሳያ መሆኑን፤ ቁርኣንን በድብቅ የሚያነብ ምፅዋት በድብቅ እንደሚሰጥ አምሳያ መሆኑን ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ድምፅን ከፍ አድርጎ ወደ ማንበብ ያነሳሳን ጥቅምና ጉዳይ ከሌለ ለምሳሌ ቁርኣንን ማስተማር ይመስል፤ ምፅዋትን መደበቅ በላጭ እንደሆነው ሁሉ ቁርኣንንም በዝግታ ማንበብ በላጭ ነው። ይህም ኢኽላስና ከይዩልኝና በራስ ከመደነቅ መራቅ ስለሚገኝበት ነው።