عن ابن عباس رضي الله عنهما قال:
جاءَ رجُلُ إلى النبي صلى الله عليه وسلم فقال: يا رسولَ اللهِ، إن أحدنا يجدُ في نفسِهِ -يُعرِّضُ بالشَّيءِ- لأَن يكونَ حُمَمَةً أحَبُّ إليه من أن يتكلَّم بِهِ، فقال: «اللهُ أكبرُ، اللهُ أكبرُ، الحمدُ لله الذي ردَّ كيدَه إلى الوسوسَةِ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والنسائي في الكبرى]
المزيــد ...

ኢብኑ ዐባስ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ብለዋል፦
አንድ ሰው ወደ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በመምጣት እንዲህ አለ፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! አንዳችን እሱን ከመናገር ይልቅ አመድ መሆን የሚያስደስተውን ነገር በነፍሱ ውስጥ ይሰማዋል።" እርሳቸውም፦ "አላሁ አክበር አላሁ አክበር የሰይጣንን ተንኮል ወደ ጉትጎታ የመለሰው አላህ ምስጋና ይገባው።" አሉ።

Sahih/Authentic. - [Abu Dawood]

ትንታኔ

አንድ ሰው ወደ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በመምጣት እንዲህ አለ፦ የአላህ መልክተኛ ሆይ! አንዳችን በነፍሱ ውስጥ የሚመላለስ ነገርን በውስጡ ይሰማዋል። ነገር ግን እሱን ከመናገር ይልቅ አመድ መሆን እስኪመኝ ድረስ እሱን መናገር ይከብደዋል። መልክተኛውም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሁለት ጊዜ ተክቢር በማሰማት የሰይጣንን ተንኮል ወደ ጉትጎታ ብቻ በመመለሱ አላህን አመሰገኑ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሰይጣን፥ አማኞችን ከአማኝነት ወደ ክህደት ለመለወጥ በጉትጎታው እንደሚጠባበቃቸው መገለፁ።
  2. ሰይጣን የኢማን ባለቤቶች ላይ ከጉትጎታ የዘለለ ምንም ነገር ማድረግ አለመቻሉ፤ በኢማን ባለቤቶች ላይ ደካማ አቅም ያለው መሆኑን ይገልፅልናል።
  3. አማኝ ከሰይጣን ጉትጎታ መሸሽና መከላከል የሚገባው መሆኑን።
  4. አስደሳች ነገር ወይም የሚያስደንቀንና የመሳሰሉት አጋጣሚዎች ሲያጋጥሙን ተክቢር ማለት የተደነገገ መሆኑ።
  5. አንድ ሙስሊም ግራ ያጋባውን ጉዳይ ሁሉ የእውቀት ባለቤቶቹን መጠየቅ የተደነገገ መሆኑን እንገነዘባለን።