عن عقبة بن عامر رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«أَحَقُّ الشُّرُوطِ أَنْ تُوفُوا بِهِ مَا اسْتَحْلَلْتُمْ بِهِ الْفُرُوجَ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከዑቅበህ ቢን ዓሚር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ:
'ልታሟሉት ከሚገቡ መስፈርቶች ሁሉ ልታሟሉት እጅግ የተገባው ብልትን ሐላል ያደረጋቹበትን መስፈርት ነው።'"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መሙላቱ እጅግ የተገባው መስፈርት በሴት መጠቀምን ሐላል ለማድረግ ሰበብ የሆነውን መስፈርት መሆኑን እየነገሩን ነው። ይህም ሚስት በጋብቻው ውል ወቅት የምታስቀምጣቸው የተፈቀዱ መስፈርቶች ናቸው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሐላልን ሐራም ሐራምን ሐላል ከሚያደርጉ መስፈርቶች በስተቀር ከሁለቱ ጥንዶች መካከል አንዱ ለሌላው ቃል የገባውን መስፈርቶች መሙላት ግዴታ ነው።
  2. የኒካሕን መስፈርቶች ማሟላት ከሌላ መስፈርቶች የበለጠ ሊሟላ የሚገባው ነው። ምክንያቱም እነዚህ መስፈርቶች ብልትን ሐላል ለማድረግ የሚገቡት ቃል ነውና።
  3. ኢስላም የጋብቻ መስፈርቶችን እንዲጠበቁ አፅንኦት መስጠቱ ጋብቻ በኢስላም ውስጥ ያለው ደረጃ ከፍ ያለ መሆኑን ያስረዳል።