عن أبي موسى رضي الله عنه أن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«لا نِكَاحَ إِلّا بِوَليٍّ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي وابن ماجه وأحمد]
المزيــد ...

ከአቡ ሙሳ (ረዲየላሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ፦
"ያለ ወሊይ ፈቃድ ጋብቻ የለም።"

Sahih/Authentic. - [Ibn Maajah]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አንዲት ሴት የጋብቻዋን ውል ለማሰር ሀላፊነት በሚወስድ ወሊይ ካልሆነ በስተቀር ጋብቻ መፈፀም እንደማይበቃላት ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የወሊይ መኖር ጋብቻው ትክክለኛ እንዲሆን መስፈርት ነው። ያለ ወሊይ ወይም ሴቲቱ ራሷን ብትድር ጋብቻው አይበቃም።
  2. ወሊይ የሚሆነው ወደ ሴቷ እጅግ ቅርብ ዘመድ የሆነ ወንድ ነው። ከርሱ የቀረበ ወሊይ እያለ ሩቅ የሆነ ወሊይ እሷን ማጋባት አይችልም።
  3. ወሊይ ለመሆን የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይገባዋል: - አቅመ አዳምና የአይምሮ ጤነኛ (ሙከለፍ) መሆን፣ ወንድ መሆን፣ የጋብቻን ጥቅም የሚያውቅ አስተዋይ መሆኑ (ቂላቂል አለመሆን) ፣ ወሊዩና ተጋቢዋ ተመሳሳይ እምነት መከተላቸው ነው። እነዚህን ባህሪያቶች ያልተላበሰ የጋብቻን ውል በማሰር ረገድ ለወሊይነት የተገባ አይደለም።
ተጨማሪ