عَنْ عَائِشَةَ أُمِّ المؤمنين رضي الله عنها:
أَنَّ أُمَّ سَلَمَةَ ذَكَرَتْ لِرَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ كَنِيسَةً رَأَتْهَا بِأَرْضِ الْحَبَشَةِ، يُقَالُ لَهَا مَارِيَةُ، فَذَكَرَتْ لَهُ مَا رَأَتْ فِيهَا مِنَ الصُّوَرِ، فَقَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «أُولَئِكَ قَوْمٌ إِذَا مَاتَ فِيهِمُ الْعَبْدُ الصَّالِحُ، أَوِ الرَّجُلُ الصَّالِحُ، بَنَوْا عَلَى قَبْرِهِ مَسْجِدًا، وَصَوَّرُوا فِيهِ تِلْكَ الصُّوَرَ، أُولَئِكَ شِرَارُ الْخَلْقِ عِنْدَ اللهِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

የአማኞች እናት ከሆነችው ከዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው፦
ኡሙ ሰላማ ለአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሀበሻ ምድር ማሪያህ በምትባል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስላየቻቸው ምስሎች ነገረቻቸው። የአላህ መልዕክተኛም ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፡- "እነዚህ ከመካከላቸው መልካም (ጻድቅ) ባርያ ወይም መልካም ሰው ሲሞት በመቃብሩ ላይ መስገጃን የሚገነቡ፤ በውስጡም (ምስሉን) ስእላ ስእል የሚቀርፁ ናቸው። እነዚህ ህዝቦች አላህ ዘንድ እጅግ ክፉ (መጥፎ) ፍጡራን ናቸው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የአማኞች እናት ኡሙ ሰለማ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - በሐበሻ ምድር ማሪያህ የምትባል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስእሎች፣ ጌጦችና ቅርፆች ማየቷን በመደነቅ ለነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አወሳች። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የነዚህን ስእሎች መደረግ ምክንያት ገለፁ። "እነዚህ አሁን አንቺ የምታወሺያቸው በመካከላቸው ደግ ሰው የሞተ ጊዜ በቀብሩ ላይ መስጂድ ይገነቡና በውስጡ ይሰግዱበታልም እነዚህንም ስእሎች ይስላሉ።" አሉ። ይህንን የሚፈጽም ሰው አላህ ዘንድ ክፉ ፍጡር እንደሆነ ገለፁ፤ ምክንያቱም ይህ ድርጊቱ በአላህ ወደ ማጋራት ስለሚያዳርስ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ወደ ሺርክ የሚያደርስን መንገድ ለመዝጋት ሲባል በመቃብሮች ላይ መስጊዶች መገንባት ወይም እርሷ ዘንድ መስገድ ወይም መስጊድ ውስጥ ሟቾችን መቅበር ክልክል ነው።
  2. መቃብሮች ላይ መስጂዶችን መገንባትና ስእሎችን መስጅድ ውስጥ መስቀል የአይሁድና ክርስቲያኖች ስራ መሆኑንና ይህንን የፈፀመም ከነርሱ ጋር መመሳሰሉን እንረዳለን።
  3. ነፍስ ያላቸውን ነገሮች ስእል መያዝ ክልክል መሆኑ።
  4. ቀብር ላይ መስጂድ የገነባ፣ መስጂድ ውስጥም (ነፍስ ያላቸው) ስእሎችን የሳለ ሰው ከክፉዎቹ የአላህ ፍጡሮች መካከል ነው።
  5. ሸሪዓ ወደ ሺርክ የሚያደርሱ መንገዶችን ባጠቃላይ በመዝጋቱ ሸሪዓ የተውሒድን ዳር ድንበር ሙሉ ለሙሉ መጠበቁን እንረዳለን።
  6. በደጋጎች ላይ ወሰን ማለፍ ሺርክ ላይ ለመውደቅ ምክንያት ስለሆነ ክልክል ነው።