+ -

عَنْ أَنَسٍ رَضيَ اللهُ عنه أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لَا تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يَتَبَاهَى النَّاسُ فِي الْمَسَاجِدِ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والنسائي وابن ماجه] - [سنن أبي داود: 449]
المزيــد ...

ከአነስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"ሰዎች በመስጂድ ጉዳይ ሳይፎካከሩ ሰዓቲቱ አትቆምም።"

[ሶሒሕ ነው።] - - [ሱነን አቡዳውድ - 449]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ከትንሳኤ ቀን መቅረብና የዱንያ መጠናቀቅ ምልክቶች መካከል አንዱ ሰዎች መስጂዶችን በማስዋብ መፎካከራቸው ነው። ወይም አላህን ከማውሳት ውጪ ለሌላ አላማ ባልተገነቡ መስጂዶች ውስጥም በዱንያቸው መፎካከራቸው ነው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በመስጂዶች መፎካከር ክልክል መሆኑን እንረዳለን። ለአላህ ተብሎም ስላልተሰራ ተቀባይነት የሌለው ስራ ነው።
  2. በቀለም፣ በቅርፃ ቅርፅና በጽሑፎች መስጂዶችን ማስጌጥ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ሰጋጆችን ሲመለከቱት ስለሚያዘናጋቸው ነው።
  3. ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "የዚህን ሐዲሥ እውነተኝነት ዛሬ ላይ መታየቱ ምስክር ይሆንልናል። እርሱም ከነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - አስደናቂ ተአምራቶች መካከል አንዱ ነው።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ