عَنْ ‌أَبِي قَتَادَةَ السَّلَمِيِّ رضي الله عنه أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«إِذَا دَخَلَ أَحَدُكُمُ الْمَسْجِدَ فَلْيَرْكَعْ رَكْعَتَيْنِ قَبْلَ أَنْ يَجْلِسَ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 444]
المزيــد ...

ከአቡ ቀታዳ አስሰለሚይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"አንዳችሁ መስጂድ የገባ ጊዜ ከመቀመጡ በፊት ሁለት ረከዓ ይስገድ።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 444]

ትንታኔ

በማንኛውም ወቅትና ለማንኛውም አላማ መስጂድ የመጣና የገባ ሰው ከመቀመጡ በፊት ሁለት ረከዓ እንዲሰግድ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አነሳሱ። ይኸውም ሁለቱ የተሒየተል መስጂድ ረከዓዎች ናቸው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከመቀመጥ በፊት የተሒየተል መስጂድ ሁለት ረከዓ መስገድ እንደሚወደድ እንረዳለን።
  2. ይህ ትእዛዝ መቀመጥ ለፈለገ ሰው ነው። መስጂድ ገብቶ ሳይቀመጥ የወጣን ሰው ትእዛዙ አይመለከተውም።
  3. አንድ ሰጋጅ ሰዎች ሶላት ውስጥ ሆነው መስጂድ ቢገባና ቀጥታ እነርሱ ወደሚሰግዱት ሶላት ቢገባ ከሁለቱ የተሒየተል መስጂድ ረከዓ ያብቃቃዋል።
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ቋንቋ: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ተጨማሪ (57)