عَنْ ‌أَبِي حُمَيْدٍ أَوْ عَنْ ‌أَبِي أُسَيْدٍ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«إِذَا دَخَلَ أَحَدُكُمُ الْمَسْجِدَ فَلْيَقُلِ: اللَّهُمَّ افْتَحْ لِي أَبْوَابَ رَحْمَتِكَ، وَإِذَا خَرَجَ فَلْيَقُلِ: اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ مِنْ فَضْلِكَ».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቡ ሑመይድ ወይም አቡ ኡሰይድ እንደተዘገበው እንዲህ አለ: "የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
‹አንዳችሁ መስጂድ የገባ ጊዜ: 'አልላሁምመፍተሕ ሊ አብዋበ ረሕመቲከ' (ትርጉሙም: አላህ ሆይ! ለኔ የእዝነትህን በሮች ክፈትልኝ) ይበል። የወጣ ጊዜም ‘አልላሁምመ ኢኒ አስአሉከ ሚን ፈድሊክ' (ትርጉሙም: አላህ ሆይ! እኔ ከትሩፋትህ እጠይቅሀለሁ።) ይበል።›"

Sahih/Authentic. - [Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መስጂድ በሚገባ ወቅት የሚባለውን ዱዓ ለኡመታቸው ጠቆሙ። (አልላሁምመ ኢፍተሕ ሊ አብዋበ ረሕመቲክ) (አላህ ሆይ! ለኔ የእዝነትህን በሮች ክፈትልኝ) የእዝነትን ምክንያቶች ለርሱ እንዲያመቻችለት አላህን ይጠይቃል። ከመስጂድ ለመውጣት የፈለገ ጊዜም (አልላሁምመ ኢኒ አስአሉከ ሚን ፈድሊክ) (አላህ ሆይ! እኔ ከትሩፋትህ እጠይቅሀለሁ።) ይበል። አላህን ከችሮታውና ከሐላል ሲሳዩ ተጨማሪ ፀጋዎቹን ይጠይቃል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ወደ መስጂድ በሚገባ ወቅትና ከመስጂድ በሚወጣ ወቅት ይህን ዱዓ ማድረግ እንደሚወደድ እንረዳለን።
  2. ሲገባ እዝነትን በመጠየቅ ላይ ሲወጣ ደሞ ችሮታን በመጠየቅ ላይ የተገደበው: መስጂድ የሚገባ ሰው ወደ አላህና ወደ ጀነት በሚያቃርበው ነገሮች ላይ ነው የሚጠመደው ስለዚህ ከቦታው ጋር የሚስማማው እዝነትን መጠየቅ ነው። የወጣ ጊዜ ደሞ ከሲሳይ የአላህን ችሮታ ለመፈለግ በምድር ላይ ስለሚሯሯጥ ከቦታው ጋር የሚስማማው ችሮታ መወሳቱ ነው።
  3. እነዚህ ዚክሮች የሚባሉት መስጂድ መግባትና መውጣት ሲፈለግ እንደሆነ እንረዳለን።