+ -

عن أبي مَرْثَدٍ الغَنَوِيّ رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«لَا تَجْلِسُوا عَلَى الْقُبُورِ، وَلَا تُصَلُّوا إِلَيْهَا».

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከአቡ መርሠድ አልጘነዊይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:
'መቃብሮች ላይ አትቀመጡ! ወደርሷም አትስገዱ!'"

ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መቃብሮች ላይ ከመቀመጥ ከለከሉ።
ይህም ወደ መቃብሮች ከመስገድ እንደከለከሉት ነው። ቀብሩ ወደ ሰጋጁ ቂብላ አቅጣጫ መሆኑን ይመስል ማለት ነው። ይህም የተከለከለው ወደ ሺርክ ከሚያዳርሱ ምክንያቶች አንዱ ስለሆነ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية القيرقيزية النيبالية اليوروبا الليتوانية الدرية الصومالية الكينياروندا
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በሐዲስ እንደተረጋገጠው የጀናዛ ሶላት ካልሆነ በቀር በመቃብር ስፍራ ወይም በመቃብሮች መካከል ወይም ወደ መቃብር ዙሮ መስገድ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. ወደ መቃብር መስገድ የተከለከለው የሺርክን መዳረሻዎች ለመዝጋት ነው።
  3. ኢስላም በመቃብር ወሰን ማለፍንም መቃብር ማዋረድንም ከልክሏል። ወሰን ማለፍም ማሳነስም የለምና።
  4. ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "የሙትን አጥንት መስበር በህይወት እንደመስበር ነው።" ስላሉ የሙስሊም ክብር ከሞተ በኋላም ዘላቂ ነው።