عن أنس بن مالك رضي الله عنه عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
«مَنْ نَسِيَ صَلَاةً فَلْيُصَلِّ إِذَا ذَكَرَهَا، لَا كَفَّارَةَ لَهَا إِلَّا ذَلِكَ: {وَأَقِمِ الصَّلاةَ لِذِكْرِي} [طه: 14]».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአነስ ቢን ማሊክ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦
"ሶላትን የረሳ ሰው ባስታወሰው ጊዜ ይስገድ። ከዚህ በቀር ማካካሻ የለውም። {ሶላትንም (በርሷ) እኔን ለማስታወስ ስገድ።} [ጣሀ:14]

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የትኛውንም የግዴታ ሶላት ወቅቱ እስኪወጣ ድረስ መስገድን የረሳ ሰው ባስታወሰ ወቅት ቀዿእ ለማድረግ መፍጠን እንደሚገባው፤ አንድ ሙስሊም በወቅቱ መስገድን በመተዉ ለፈፀመው ወንጀልም ባስታወሰ ወቅት መስገዱ እንጂ ሌላ ምንም ማበሻና ማስማሪያ እንደሌለው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ገለፁ። አላህ በተከበረው መጽሐፉ እንዲህ ብሏል {ሶላትንም (በርሷ) እኔን ለማስታወስ ስገድ።} [ጣሀ:14] ማለትም የተረሳን ሶላት ባስታወስካት ወቅት ቀጥ አድርገህ ስገድ ማለትም ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የሶላት አንገብጋቢነት እና በወቅቱ ከመፈፀምና ቀዿእ ከማድረግ መሳነፍ እንደማይገባ መገለፁን እንረዳለን።
  2. ያለሸሪዓዊ ምክንያት ሶላትን ከወቅቱ ሆን ብሎ ማዘግየት እንደማይፈቀድ እንረዳለን።
  3. የረሳ ሰው ባስታወሰ ወቅት፣ የተኛ ሰው ደግሞ በነቃ ወቅት ሶላትን ቀዷእ ማድረግ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
  4. በተከለከለ ወቅት እንኳን ቢሆን ሶላትን በፍጥነት ቀዿእ ማድረግ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።