عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«مَنْ يُرِدِ اللهُ بِهِ خَيْرًا يُصِبْ مِنْهُ».

[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 5645]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ ለርሱ መልካም የሻለትን ሰው ይፈትነዋል።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 5645]

ማብራሪያ

አላህ በአንድ አማኝ ባሪያው ላይ መልካምን የፈለገ ጊዜ በነፍሳቸው፤ በገንዘባቸውና በቤተሰቦቻቸው እንደሚፈትናቸው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ተናገሩ። ይህም አንድ አማኝ በሱ ምክንያት ወደ አላህ በዱዓእ መጠጋት፣ የወንጀል መማርና የደረጃ ከፍ ማለትን ስለሚያገኝ ነው።

ከሐዲሡ የሚቀሰሙ ቁምነገሮች

  1. አማኝ የሆነ ሰው ለተለያዩ የመከራ አይነቶች የተጋለጠ ነው።
  2. ፈተና የአንድ አማኝን ደረጃ ከፍ ከማድረጉ፣ ማዕረጉን ከመስቀሉና ወንጀሉን ከማስማሩ አኳያ አላህ ለባሪያው ላለው ውዴታ ምልክት ሊሆን ይችላል።
  3. በመከራዎች ላይ ትእግስት በማድረግና ባለመበሳጨት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
ትርጉሞችን አሳይ
ቋንቋ: الإنجليزية الأوردية الإسبانية ተጨማሪ (68)
ተጨማሪ