عن قيس بن عاصم رضي الله عنه قال:
أتيتُ النبيَّ صلى الله عليه وسلم أُريدُ الإسلامَ، فأَمَرَني أن أغتَسِلَ بماءٍ وسِدرٍ.

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي]
المزيــد ...

ከቀይስ ቢን ዓሲም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦
"ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ እስልምናን መቀበል ፈልጌ መጣሁ። እሳቸውም በውሃና በቁርቁራ ቅጠል እንድታጠብ አዘዙኝ።"

Sahih/Authentic. - [Abu Dawood]

ትንታኔ

ቀይስ ቢን ዓሲም ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እስልምናን መቀበል ፈልጎ መጣ። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በውሃ እና ቅጠሉን ለማንፃት በሚገለገሉበትና ጥሩ መአዛ ባለው የቁርቁራ ዛፍ ቅጠል እንዲታጠብ አዘዙት።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ካፊር ወደ እስልምና በሚገባ ወቅት መታጠቡ የተደነገገ መሆኑን እንረዳለን።
  2. የእስልምና ደረጃንና ለነፍስም ሆነ ለአካልም ትኩረት መስጠቱን እንረዳለን።
  3. ውኃ ንፁህ ከሆኑ ነገሮች ጋር መቀላቀሉ ከጠሀራነት አያስወጣውም።
  4. ሳሙናና የመሳሰሉት ዘመን አመጣሽ የሆኑ ማፅጃዎች የቁርቁራ ቅጠልን ቦታ ይተካሉ።