عن أبي هريرة قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«حَقٌّ عَلَى كُلِّ مُسْلِمٍ أَنْ يَغْتَسِلَ فِي كُلِّ سَبْعَةِ أَيَّامٍ يَوْمًا، يَغْسِلُ فِيهِ رَأْسَهُ وَجَسَدَهُ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: "የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"እያንዳንዱ ሙስሊም በየሰባት ቀኑ አንድ ጊዜ ገላውን መታጠብ አለበት። ሲታጠብም ጭንቅላቱንም ገላውንም መታጠብ አለበት።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁሉም ለአቅመ አዳምና የደረሰና አዕምሮው ጤነኛ በሆነ ሙስሊም ላይ ሁሉ በሳምንት ውስጥ ካሉት ሰባት ቀናት አንዱን ቀን የመታጠብ የጠበቀ ሀቅ እንዳለበት ተናገሩ። በዚህ ቀንም ንፅህናንና ፅዳትን በመፈለግ ጭንቅላቱንና ሰውነቱን ይታጠባል። ይህንን ሀሳብ ከሚያንፀባርቁ አንዳንድ ዘገባዎች እንደምንረዳው ከነዚህ ቀናቶች ሁሉ ለመታጠብ በላጩ ቀን የጁሙዐ ቀን ነው። ለምሳሌ ያህል ሀሙስ ቀን እንኳ ታጥቦ የጁሙዐ ቀን ከሶላት በፊት መታጠቡ አፅንኦት የተሰጠው ተወዳጅ ጉዳይ ነው። የጁሙዐ ቀን መታጠብን ከግዴታነት የሚያዞረው (ግዴታ አለመሆኑን የሚያሳየው) የእናታችን ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና እንዲህ የሚለው ንግግር ነው "ሰዎች ነፍሶቻቸውን ለመቀለብ የሚሰሩ ነበሩ። ወደ ጁሙዐ የመጡ ጊዜም በዛው በስራ ድባባቸው ይመጡ ነበር። ለነርሱም 'ብትታጠቡስ' ተባሉ።" (ቡኻሪ ዘግበውታል) በሌላ ዘገባቸው "እየሸተቱም ይመጡ ነበር።" ማለትም የላብና የመሳሰሉት ሽታ እየሸተቱ ይመጡ ነበር። ከዚህ ሁኔታቸው ጋርም ሆነው "ብትታጠቡስ" መባላቸው ከነርሱ ውጪ ያለው ግዴታው ላይሆን ይበልጥ የተገባ ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ኢስላም ለንፅህናና ፅዳት ትኩረትና ቦታ መስጠቱን እንረዳለን።
  2. የጁሙዐ ቀን ለሶላቱ ብሎ መታጠብ አፅንኦት የተሰጠው ተወዳጅ ጉዳይ ነው።
  3. ገላን መታጠብ ሲባል ጭንቅላትም አብሮ ቢካተትም፤ ለብቻው የተጠቀሰው ትኩረት እንዲሰጠው ነው።
  4. ሰዎች በሚታወኩበት መልኩ መጥፎ ጠረን ያለበት ሰው የመታጠብ ግዴታ አለበት።
  5. ከመታጠቢያ ቀናቶች ሁሉ ተወዳጅነቱ የጠነከረ የሆነው ቀን ጁሙዐ ነው። ይህም ቀኑ ብልጫ ስላለው ነው።