+ -

عَن أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«يُسَلِّمُ الرَّاكِبُ عَلَى المَاشِي، وَالمَاشِي عَلَى القَاعِدِ، وَالقَلِيلُ عَلَى الكَثِيرِ». وَلِلبُخَارِي: «يُسَلِّمُ الصَّغِيرُ عَلَى الكَبِيرِ، وَالمَارُّ عَلَى القَاعِدِ، وَالقَلِيلُ عَلَى الكَثِيرِ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 6232]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ "የአላህ መልዕክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
"የሚጋልብ ሰው ለእግረኛ ሰላምታን ያቅርብ፤ እግረኛ ለተቀማጭ ሰላምታን ያቅርብ፤ ጥቂት ሰዎች በብዙ ሰዎች ላይ ሰላምታን ያቅርቡ።'"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 6232]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሰዎች መካከል "አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱሏሂ ወበረካቱሁ" የሚለውን ሰላምታን የማቅረብ ስነ-ስርዓትን ጠቆሙ። ይኸውም ህፃን ለትልቅ፣ ጋላቢ ለእግረኛ፣ እግረኛ ለተቀማጭ፣ ጥቂት ቁጥር ያላቸው በብዙዎቹ ላይ ሰላምታን ያቅርቡ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሐዲሥ ላይ በመጣው መልኩ ሰላምታን ማቅረብ እንደሚወደድ እንረዳለን። ነገር ግን እግረኛ ለጋላቢ ወይም ከዚህም ውጪ ሐዲሡ ላይ ከተጠቀሰው በተቃራኒው ሰላምታ ቢያቀርብ ከበላጩና ከተሻለው ተቃራኒ ቢሆንም ይፈቀዳል።
  2. በሐዲሡ ላይ በተጠቀሰው አፈፃፀም መልኩ ሰላምታን ማስፋፋት ውዴታንና ትስስርን ከሚያመጡ ነገሮች መካከል አንዱ ነው።
  3. በሐዲሡ ላይ የተጠቀሱት ተመሳሳይና ተመጣጣኝ ከሆኑ በላጩ ሰው ሰላምታውን የሚጀምረው ነው።
  4. የሰው ልጅ የሚያስፈልገውን ሁሉ በማብራራት ረገድ የሸሪዓን ምሉዕነት እንረዳለን።
  5. የሰላምታን ስነ-ስርዓት ማስተማርና ለሁሉም የሚገባውን ሐቅ (መብት) መስጠት እንደሚገባ እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية Kyrgyzisht النيبالية Jorubisht الليتوانية الدرية الصربية الصومالية Kinjaruandisht الرومانية المجرية التشيكية الموري Malagasisht Kannadisht الولوف Azerisht الأوكرانية الجورجية المقدونية
ትርጉሞችን ይመልከቱ