عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ:
أَلَسْتُمْ فِي طَعَامٍ وَشَرَابٍ مَا شِئْتُمْ؟ لَقَدْ رَأَيْتُ نَبِيَّكُمْ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وَمَا يَجِدُ مِنَ الدَّقَلِ مَا يَمْلَأُ بِهِ بَطْنَهُ.
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2977]
المزيــد ...
ከኑዕማን ቢን በሺር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል:
"እናንተ የምትፈልጉትን ምግብና መጠጥ እየተመገባችሁ አይደልንዴ? ነቢያችሁን -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሆዳቸውን የሚሞሉበት የሆነ የወረደ ተምርን እንኳ ሳያገኙ ቀርተው ተመልክቻቸዋለሁ።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2977]
ኑዕማን ቢን በሺር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ሰዎች ያሉበት ፀጋ የፈለጉትን ያህል የሚበሉና የሚጠጡበት ሁኔታ ላይ እንዳሉ ገልፀው ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ግን ረሃባቸውን ለማስታገስ ሆዳቸውን የሚሞላ የወረደ ተምርን እንኳ የማያገኙበት ሁኔታ ላይ እንደነበሩ ተናገረ።