+ -

عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ:
أَلَسْتُمْ فِي طَعَامٍ وَشَرَابٍ مَا شِئْتُمْ؟ لَقَدْ رَأَيْتُ نَبِيَّكُمْ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وَمَا يَجِدُ مِنَ الدَّقَلِ مَا يَمْلَأُ بِهِ بَطْنَهُ.

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2977]
المزيــد ...

ከኑዕማን ቢን በሺር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል:
"እናንተ የምትፈልጉትን ምግብና መጠጥ እየተመገባችሁ አይደልንዴ? ነቢያችሁን -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሆዳቸውን የሚሞሉበት የሆነ የወረደ ተምርን እንኳ ሳያገኙ ቀርተው ተመልክቻቸዋለሁ።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2977]

ትንታኔ

ኑዕማን ቢን በሺር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ሰዎች ያሉበት ፀጋ የፈለጉትን ያህል የሚበሉና የሚጠጡበት ሁኔታ ላይ እንዳሉ ገልፀው ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ግን ረሃባቸውን ለማስታገስ ሆዳቸውን የሚሞላ የወረደ ተምርን እንኳ የማያገኙበት ሁኔታ ላይ እንደነበሩ ተናገረ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የነበሩበትን የዱንያ ዛሂድነት (ቸልተኝነት) መገለፁ።
  2. ከዱንያ ዛሂድ (ቸልተኛ) በመሆን፣ ዱንያን በማሳነስና ነቢዩን -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በመከተል ላይ መነሳሳቱን እንመለከታለን።
  3. ሰዎች ያሉበትን ፀጋ በማስታወስና አላህንም በማመስገን ላይ መተዋወስ እንደሚገባ መነሳሳቱን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية المقدونية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ